Voice Of Dilla /VOD/

Voice Of Dilla /VOD/ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Voice Of Dilla /VOD/, Grocers, Dubai.

09/09/2025

‎የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ተመስገን ጥላሁን (ኢንጂነር) ያስተላለፉት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት፦

‎የአንድነታችን አርማ የኢትዮጵያዊያን ተጨማሪ የወል እውነት የሕዳሴ ግድብ ምረቃ በዓል እንኳን አደረሰን!

‎መላው ኢትዮጵያውያን በቁጭት ተነስተው ካላቸው ሳይሆን ከሌላቸው አጉድለው በባለቤትነት የገነቡት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያዊያን ከብርሃንም በላይ ነው።

‎በአምስት አመት ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ተወጥነው የተጀመረው ግድባችን ግንባታው እንዳይሳካ በውጭ የኢትዮጵያ ታርካዊ ጠላቶች በውስጥ ሀገርን የሚሸጡ ባንዳዎች ተናበው ያደርጉ የነበረው አሰናካይ አካሄድ ምክንያት ተደናቅፎ ከነበረበት በመሪያችን ቁርጠኝነትና የድፕሎማሲ ጥበብ ዳግም አንሰራርተው በሚደነቅ መልኩ እነሆ እውን ሆኗል።

‎ብልጽግና ፓርቲ በ2018 ዓ/ም ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን ለመድረስ ያስቀመጠውን ግብ እውን ማድረጉን ያረጋገጠበት የሕዳሴ ግድብ ከብርሃንነት ባሻገር ለኢትዮጵያዊያን ተጨማሪ እድሎችን የሚያመጣ እንዲሆን ተደርጎ ተገንብቶ ተጠናቋል።

‎ቃልን በተግባር ከማሳየት ቦዝኖ የማያውቀው ብልጽግና ፓርቲ ከሁለት ዓመት በፊት "ኢትዮጵያ በእዳ ከመጨፍገግ ወደ በምንዳ መንበሽበሽ" ማለቱ የሚተወስ ስሆን እነሆ ቃሉን ለመፈጸም የብርሃን ጮራ መፈንጠቅ ጀምሯል።

‎ኢትዮጵያ ለዘላለም ታፍራና ተከብራ ትኑር!
‎እንኳን ደስ አለን አላችላሁ!

‎ ተመስገን ጥላሁን (ኢንጂነር)
‎ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ
‎ ጳጉሜ 04/2017 ዓ/ም

የድህረ እውነት ዜመን በኢትዮጵያ 2017 ዓ/ም
02/06/2025

የድህረ እውነት ዜመን በኢትዮጵያ 2017 ዓ/ም

Submit an appeal to challenge a content decision made by Facebook or Instagram. The Oversight Board may select and review your case.

13/02/2025
24/12/2024

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋንጫ ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ገለፀ

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ይህንን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የመግለጫዉ ሙሉ መልዕክት እንደሚከተለዉ ቀርቧል፡-

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለዘመናት የተጫነብንን የተረጂነትና የተመጽዋችነት አሳፋሪ ታሪክን ሽሮዉ በምትኩ ወደ ታላቅነት በድጋሚ መመለሳችንን ለዓለም ሕዝብ የምናበስርበት የዞናችን ብሎም የኢትዮጵያ ህዝብ አሻራ ያረፈበት ግዙፍ ፕሮጀክታችን ነዉ፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በማድረስ፣ በስራ ዕድል ፈጠራም ሆነ በለሎች የዕድገት ተሸካሞት ወሳኝ ምዕራፍ አለው፡፡

ፕሮጀክቱ የሀገራችንን ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ከማሳለጥም በተጨማሪ በምሥራቅ አፍሪካ የሚኖራትን ሁሉን አቀፍ ተጽዕኖ በማጉላት ሀገራችን የቀጠና የሃይል ቋትም ያደርጋታል፡፡

ለፕሮጀክቱ መሳካት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት 19ኛውን ኢትዮጵያ ብሔር፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል በአርባ ምንጭ ከተማ ሲከበር ታላቁ የህዳሴ ግድብ ዋንጫ ከሶማሌ ክልል ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መተላለፉ ይታወቃል፡፡

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ዋንጫ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚቆይበት ጊዜ የክልሉን ህዝብ በማስተባበር ብሔራዊ ኩራታችን ለሆነው ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ሃብት ለማሰባሰብና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማስተባበር በክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባባሪያ ጽ/ቤት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አከናዉኗል፡፡

በዚህም መሰረት የፊታችን ዕሮብ ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም. በዲላ ከተማ በጌዴኦ ዞን ባህል አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሀብት ለማሰባሰብ ክልላዊ የንቅናቄ መድረክ ማስጀመሪያ ፕሮግራምና የህዳሴውን ዋንጫ ለጌዴኦ ዞን የማስረከብ መርሃ-ግብር ተዘጋጅቷል፡፡

በዚህም ዋንጫ ለቀጣይ 30 ቀናት በዞኑ ባሉ ሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች እየተዘዋወረ የሚቆይ በመሆኑ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ለህዳሴ ግድቡ በስኬት ለማጠናቀቅ እስካሁን ሲናደርገው እንደነበረው ሁሉ በአሁኑ ወቅትም ቦንድ በመግዛት ድጋፉን አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ እዉን እንዲሆን ከዚህ ቀደም ቦንድ በመግዛትና ዋንጫዉ በዞናችን በቆየባቸዉ ወቅት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ዞኑ ከአቻ ዞኖች የላቄ ገቢ ማሰባሰብ እንደቻልነዉ ሁሉ አሁንም በአዲሱ ክልል ታቅፈን ዋንጫዉን በመቀበል በቆይታዉ የላቄ ዉጤት እንደምናስመዘግብ ባለሙሉ ተስፋ ነኝ፡፡

መላዉ በዞናችን የሚገኝ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የግድቡ ግንባታ ገቢ አሰባሰብ አስተዋፅኦ የማድረግ የገቡትን ቃል የሚፈጽሙበትና ቃል ያልገቡ የህብረተሰብ ክፍሎችም በአድስ መልክ ቃል ገብተው ርዕሰ-ጉዳዩ የሃገራችንም፣ የመንግስታችንም፣ የህዝባችንም ቀዳሚ ፕሮጀክት መሆኑን በመገንዘብ በከፍተኛ ተነሳሽነት ዋንጫውን ተቀብለን ለሌሎች አርዓያ የሚሆን ውጤት በማስመዝገብ የዞን ገፅታ በሚገነባ አፈፃፀምም ጭምር ልንሸኘው ስለሚገባን የዞናችን ህዝብ ይህንን ዕድል ተጠቅሞ ሰፊ ተሳትፎ በማድረግ አሻራውን ለማስቀመጥ ከመቼውም ጊዜ በላይ መጠነ-ሰፊ እንቅስቃሴ እንዲታደርጉና ለታላቁ ህዳሴ ግድብ አሻራችሁን እንድታሳርፉ የዞኑ መንግስት ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ፈጣር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!!

ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
ታህሳስ 14/2017 ዓ.ም

22/12/2024

"የተከበሩ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የወደፊቷ የኢትዮጵያ ተስፋ ፣ እና የብልጽግና ጉዞ አብነት እንደሚሆን ፈረንሳይ እምነቷ ነው።

ኢትዮጵያ ለሰው ልጅ መገኛነት የመጀመሪያ አሻራ ያላት ሃገር ናት:: በሁለቱ ሃገሮች መካከል ያለው ግንኙነት በታሪክ ሂደትና በትላልቅ የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ የተመሰረተ ነው።.

እ.ኤ.አ. በ 2019 መሰረታዊ የሆኑ የባህልና የቅርስ ጥበቃን ከሳይንሳዊ ፕሮግራም ጋራ አያይዘን ለመስራት ወስነን ተነስተናል።

በላሊበላም የሰራነው በዓለም ላይ ልዩ የሆነ የቅርስ ጥበቃ ፕሮጀክት በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ ፍጻሜውን የሚያገኝ ይሆናል።

በአንድ ወቅትም የብሔራዊ ቤተ መንግሥት እድሳት ፕሮጀክትንም ሰርተን ዛሬ የሚያኮራ እውነታ ሆኖ እየታየ ነው።

ወደፊትም የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዘመንን ለመደገፍ እና በትግራይ የሰላምና የመረጋጋት መሰረት የሆነውን የፕሪቶሪያ ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ ትብብር እናደርጋለን።

የተከበሩ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር Abiy Ahmed Ali የወደፊቷ የኢትዬጵያ ተስፋ እና የብልጽግና ጉዞ አብነት እንደሚሆን ፈረንሳይ እምነቷ ነው። "

:- የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን መልዕክት

ራሱን ንስር ሚዲያ እያለ ስንቀሳቀስ የነበረው ጥንብ አንሳው በቁጥጥር ስር ውለው ማረሚያ ላይ ይገኛል።
05/09/2024

ራሱን ንስር ሚዲያ እያለ ስንቀሳቀስ የነበረው ጥንብ አንሳው በቁጥጥር ስር ውለው ማረሚያ ላይ ይገኛል።

የንስር ሚዲያ ወይም ጥንብአንሳው የአሁናዊ አቋም
24/08/2024

የንስር ሚዲያ ወይም ጥንብአንሳው የአሁናዊ አቋም

እውነታው ይህ ነው ወረኞች ያኔም ዛሬም ነገም በወሬና ትችት ይቀጥላሉ እንደ ዲላ ዙሪያ ወረዳ በቅንጅት የተጀመረው ከወረዳ በገኘነው መረጃ መሠረት ባለፈው በግምገማ መድረክ ላይ የተገኙ የጌዴኦ...
24/08/2024

እውነታው ይህ ነው ወረኞች ያኔም ዛሬም ነገም በወሬና ትችት ይቀጥላሉ እንደ ዲላ ዙሪያ ወረዳ በቅንጅት የተጀመረው ከወረዳ በገኘነው መረጃ መሠረት ባለፈው በግምገማ መድረክ ላይ የተገኙ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኩቡር ዶ/ር ዝናቡ ወልደ እንደተናገሩት በዲላ ዙሪያ በግብርና በመጣ ለውጥ የምግብ ዋስትና አንዲሁም የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ሁሉ በቀጣይ በጤና በት/ት በመልካም አስተዳዳር እና በህዝብ ተጠቃምነት ላይ ጠንክራችሁ ስሩ ዞናችንንና ወረዳዎቻችን ለማፍረስ የተነሳውን የሀሰት ወረና ፕሮፓጋንዳ እና የፅንፈኞችን አመለካከት እና ጤናማ ያልሆነ አስተሳሰብ ባዶነታቸውን ትታችሁ ለህዝብ ስሩ ብላል፡፡

24/08/2024

ጥንብ አንሳው ሚዲያ ማንነቱ በመታውቅ ለማውቅ በውስጥ መስመር ጠይቁኝ

ወድ የማህበራዊ ተጠቃምዎች እንደምን ቆያችሁ የማይጠቅምና የወረደ የ21ክፍለ ዘመን ያለሆነ የወረዳ አስተሳሰብ ባለበት የሆንው ንስር ተብየሁ የጥንብ አንሳው ምስል ያስቀምጠና ራሱ ጥንብ አንሽው...
24/08/2024

ወድ የማህበራዊ ተጠቃምዎች እንደምን ቆያችሁ የማይጠቅምና የወረደ የ21ክፍለ ዘመን ያለሆነ የወረዳ አስተሳሰብ ባለበት የሆንው ንስር ተብየሁ የጥንብ አንሳው ምስል ያስቀምጠና ራሱ ጥንብ አንሽው ሚዲያ በለበት ማን እንደሆኔ ለማወቅ ባደረግነው ጥረት ለማወቅ ችለናል በመሆኑም ባሳለፍነው ጥቅት ግዜ ውስጥ በሀሰተኛ ወረ ህዝቡን በታማኝነት የምያገለገሉትን አመራሮች የስም የማጥፋት ዘመቻ ብያደረግም አሁን ወደ መቃብር ጉድጋድ እየቀረበ ይገኛል ይህንን በቅርቡ እናያለን በመቀጠል ሁላችን ይህንን ጥንብ አንሳው ልናወግዘው ይገባል ...

በመቀጠል በጣም የምገርም ነገር ለንደዝህ ተራና ለወረደ ነገር ያደርጋል ለማለት የምከብድ ግለሰብ በመሆኑ ማንነቱንና እንደት አንዳገኘነው ለማወቅ ከፈለጋችሁ ስክርን ሹት ለማወቅ ከፈለጋችሁ በውስጥ መስመር ጠይቁኝ ...

ከዛረ ጀምሮሆ ስምህ ጥንብአንሳ ነህ ሁሉም ቦታ ጥንብአንሳይ ትባላለህ

Address

Dubai

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Voice Of Dilla /VOD/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category