04/03/2026
ችግሮች በውይይት ብቻ እልባት ሊያገኙ ይገባል ብለን እናምናለን። ውጊያ አንፈልግም። ችግራችንን ተወያይተንና ተነጋግረን መፍታት የተሻለ መንገድ ነው ብለን እናምናለን። ይህን ለመፍታት ሀገራዊ የምክክር መድረክ ወሳኝ መፍትሔ ሊሆን ይችላል ብለን እናምናለን። ስለሆነም ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አቋቁመን ከሞላ ጎደል ከትግራይ ውጭ አብዛኛው ሥራ እየተገባደደ ነው።
በትግራይ ግን ውይይት እንዳይደረግ፣ ሕዝባችን ቁጭ ብሎ እንዳይወያይ፣ ጥያቄ አንስቶ መፍትሔ እንዳያገኝ፤ ያቆሞ ቀር ኃይል እያደናቀፈ ይገኛል። ይህ ደግሞ ትክክለኛ አቋም አይደለም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ካደረጉት ቆይታ የተወሰደ