20/05/2024
እኔና ተሻገር
ሃብታሙ ተካልኝ
ግንቦት 9-2016 ደሴ
ሃሳቦች ሁሉ ወደ ተሻገር ናቸው.. ይልቅ ከመንፈስ ቅዱስ ተዋልደናን የቤተክስቲያን ልጅነታችን አስተሳስሮናል የሚሉ ወንድሞችና እህቶች ለአፍታ እንኳ ስለእርሱ ከመጨነቅ ቦዝነው አያውቁም... በሃያዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ወጣት የዪንቨርስቲ ተማሪ ነው ተሸገር ..በተለይ ከፍሬሽ ማን ጀምሮ የሚውቁት ወዳጆቹ ከቤተሰቦቹ ጋር የነበረው ቆይታ ምንያህል በስነ ምግባር ታንጾ ያደገ እንደሆነ ለመገመት አልከበዳቸውም …ምክንያቱም መንፈሳዊነቱ፤ ታታሪነቱ፤ ሰው አክባሪነቱ.. ምን አለፋችሁ ተሻገር ማለት ኦርቶዶክሳዊና ሰዋዊ ቃናው ዘወትር የመንገድ አላፊውን ሁሉ ቀልብ እንደገዛው ነው….አሁን ይህ ታሪክ ከተከወነ ሁለት ዓመታት አልፈዋል በማያረጅና በውዕደቱ መሃል ወዘናው በማይወይብ የግዜ ሃዲድ እየገሰገሰ ያለው ተሻግር መሳፈሪያውን ግዜን በማንነት መሆን ያቃተው ይመስላል ….ለዚህም ነው በቅርብ የሚያውቁት ወዳጆቹ አብዝተው እሰለርሱ መጨነቃቸው….ዛሬ ያ ፍሬሽ ማን እና የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ እያለ ያሳሳ የነበረ መንፈሳዊነቱ ኮሳሷል፤ ታዛዥነቱ፤ ሰው አክባሪነቱና ትህትናው የተሰራባቸው መሰረቱ እንዳልሆኑ አሁን አሁን እንደ መስከረም ወፍ የሚናፈቁ ምግባራቱም ከሆኑ ሰነባብተዋል ….የመንፈስ ፍሬያትም ታጭደውበት በቃርሚያ ከቀረ ቆየ…..ለዚህ ነው ተሻገር ምን ነካው የሚሉ አንደበቶች የበረከቱት …. አልፎ አልፎ ከፋ ሲልበትም ሱስ ቤቶችም ይታያል … ኦ ተሻገር….
….እኔም ስለ ተሼ ከሚጨነቁ ወንድምና እህቶች መሃል እራሴን አገኘውት ….አንድ ቀን ግቢ ጉባኤያችን ከሚገለገልበት ቤተክርስቲያን ቅጥር አጸድ ስር ቁጭ ብዬ ስለ ተሼ ማሰላሰል ጀመርኩ ….ዓይነ ህሊናዬን ከጠፋው ወንድማችን ላይ ተክዬ በጥያቄ አፋጥጠው ጀመር ….ግን ምን ነካህ?…አሁን ባለህበት ህይዎት ሰላም ይሰማሃል? ….የቱ ሃይል ነው ከከፍታህ ያወረደህ? ….ከኪዳኑና ከቅዳሴው ስርዓት ተገኝቶ ከህጣኑ መዓዛ ከመካፈል ይልቅ ዓለም የአዳምን ዘር የምታጠምድበት የመጠጡና የጫቱ የከረፋ ሽታ እንዴት አድርጎ ቀልብህን ገዛው? …..እና የመሳሰሉ ጥያቄዎችን ሰነዘርኩበት …….መልስ የለም …..እንባዬ ድንገት ተወርዉሮ መሬት ጠብ ሲል ከሃሳቤ ነቃው ….ሰዓቱን ሳየው 2፤00 ይላል የትምህርት መግቢያ ሰዓታችን ስለደረሰ ወድያው ከተቀመጥኩበት የዛፍ ግንዳፊና የትካዜ ዙፋን ብድግ ብዬ አቡነ ዘበሰማያት ልደግም ተሰናዳው …….ወዴት ወዴት አለኝ አዕምሮዬ ….ደነገጥ …እውነት ተሻገር ነህ አንተ የሚለቀስለት? አለኝ አዕምሮዬ ….እንዴት? አልኩ ሙግት መግጠም ሳልፈልግ አዕምሮዬን ገጠምኩት …..ስንት ለሰው የማይታይ የፈረሰ ጎን አለህ?…..ስንትስ ግዜ በስንፍና: በቸልተኝነት የሚወድህ አምላክህን ልቡን አቁስለኸዋል? ….ቀጠለ … ….ስለተሼ እንቅልፍ ያጣችሁ ወንድምና እህቶቼ ስለኔም ጭራችሁ አንቡ››…………ድጋሚ ከሃሳቤ ብንን ብዬ አቡነ ዘበሰማያቴን አድርሼ ወደ ዩንቨርሲቲያችን አመራሁ….