የአሶሳ ከተማ አስ/ር ሠላም ግንባታ ፀጥታ መምሪያ

የአሶሳ ከተማ አስ/ር ሠላም ግንባታ ፀጥታ መምሪያ public Service

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ም/ቤት በአሶሳ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ጸጥታ ዙሪያ ውይይት በማድረግ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡****************************************...
04/12/2023

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ም/ቤት በአሶሳ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ጸጥታ ዙሪያ ውይይት በማድረግ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡
**********************************************
(ህዳር 24/16ዓም አሶሳ)
የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ም/ቤት በአሶሳ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች ጸጥታ ዙሪያ ውይይት በማድረግ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡

የጸጥታ ም/ቤት ስብሰባውን የመሩት ክቡር ከንቲባ አቶ አብደልከሪም አብደረሂም፤ የአሶሳ ዞን መስ/ር ም/ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዑስማን መሐመድ፤የቤ/ጉ/ክ ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር አምሳሉ አሪና እና የቤ/ጉ/ሚ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኦሳም የሱፍ ጋር በጋራ በመሆን ሲሆን የአሶሳ ከተማ አስተዳደር እና አጎራባች ወረዳዎችን ጸጥታ ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ በመወያየት
የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፈዋል፡-
**********
1ኛ/ማንኛውም ሰሌዳ የሌላቸው ባጃጆች፣የሞተር ብስክሌትና መኪና በማንኛውም ሠዐት እንዳይንቀሳቀ፤

2ኛ/በአሶሳ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ከምሽቱ ከ2፡00 እስከ ንጋቱ 12:00 ባጃጅና የሞተር ብስክሌት ከተፈቀደላቸውና ወደ ህክምና ከሚያጓጉዙ ውጪ የእንቅስቃሴ ገደብ የተጣለ መሆኑ.፤

3ኛ/ በአሶሳ ከተማ የሚገኙ የጭፈራና መጠጥ ቤቶች ከምሽቱ 4:00 ጀምሮ እንዲዘጉ የሠዐት ገደብ የተጣለ መሆኑ

4ኛ/ የቤት አከራዮች የተከራዮቻቸውን መረጃ ለቀበሌያቸው እንዲያሳውቁ፤በማያሳውቁ አከራዮች ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን፤

5ኛ/የሆቴል አልጋ አከራዮች ህጋዊ የታደሠ መታወቂያ ያላቸውን ደንበኞች ብቻ እንዲያከራዩ፤አጠራጣሪ መረጃዎችን ሲያገኙ ወዲያውኑ ለቅርብ የጸጥታ አካላት እንዲያሳውቁ ፤

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር፣የአሶሳ ዞን፣የቤ/ጉ/ክ/ፖሊስ ኮሚሽንና የቤ/ጉ/ሚሊሻ ጽ/ቤት ጥምር ጸጥታ ም/ቤት ውሳኔ ያስተላለፈ ሲሆን ለተፈጻሚነት ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ከ25/03/16ዓም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሚፈጸም፤ ሁኔታዎች እየተገመገሙ ማሻሻያ የሚደረግ ሆኖ በየደረጃው እስከ ቀበሌ ድረስ ያለው የጸጥታ መዋቅርና ዘወትር ለጸጥታ ተባባሪ የሆነው የአሶሳ ከተማአስተዳደርና አጎራባች ወረዳዎች የበኩላቸውን እንዲያስፈጽሙ ተወስኗል፡፡

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ አሶሳ ከተማ ገቡ***************(አሶሳ፣ ህዳር 22/2016 ዓ.ም) የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ቤኒሻንጉል...
02/12/2023

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ አሶሳ ከተማ ገቡ
***************

(አሶሳ፣ ህዳር 22/2016 ዓ.ም) የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ገብተዋል።

አቶ ታገሰ ጫፎ አሶሳ ህዳሴ ኤርፖርት ሲደርሱም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ ም/ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ፣ የክልሉ ም/ቤት አፈ-ጉባኤ ዶ/ር ተመስጌን ዲሳሳ፣ ብልጽግና ዋና መስሪያ ቤት የፖለለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ሀላፊ አቶ ሙሳ አህመድ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ኢሳቅ አብደልቃድርን ጨምሮ ከፍተኛ የክልል የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታም "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል በአሶሳ የስልጠና ማዕከል እየተሰጠ ያለውን የመንግስት አመራሮች ስልጠና ማጠቃለያ እና በክልሉ እየተሰሩ የሚገኙ፣ የልማት ስራዎችን ተዘዋዉረው ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Address

Assosa
Addis Ababa
100000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአሶሳ ከተማ አስ/ር ሠላም ግንባታ ፀጥታ መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category