Arada sub city woreda 2 womens lig/አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ሴቶች ሊግ

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Arada sub city woreda 2 womens lig/አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ሴቶች ሊግ

Arada sub city woreda 2 womens lig/አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ሴቶች ሊግ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Arada sub city woreda 2 womens lig/አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ሴቶች ሊግ, Grocers, Addis Ababa.

የሴቶች አደረጃጀት ተቋም በማጠናከር ለጠንካራ ፓርቲ መመስረት ተግቶ መስራት ይገባል!!!        አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያምበብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሴቶች ክንፍ የ3ተኛ ሩብ ዓ...
02/05/2025

የሴቶች አደረጃጀት ተቋም በማጠናከር ለጠንካራ ፓርቲ መመስረት ተግቶ መስራት ይገባል!!!
አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያም

በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሴቶች ክንፍ የ3ተኛ ሩብ ዓመት ኮንፈረንስ በደመቀ መልኩ አከናወነ።

የሴቶች አደረጃጀት ተቋም በማጠናከር ለጠንካራ ፓርቲ መመስረት ተግቶ በመስራት የሴቷ የውሳኔ ሰጪነት ሚና የበለጠ ማረጋገጥ ላይ ተግቶ መስራት እንደሚገባ በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊና የእለቱ የክብር እንግዳ አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያም ገልጿል።

ሴቶች የሀገር ግንባታ ሚና ግንባር ቀደም ሚና እንዳላቸው የገለፁት አቶ ተወዳጅ ይህ የበለጠ ከፍ ለማድረግ በሁሉም ዘርፎች የሴቶች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ አመላክቷል።

ሴቶች ለሀገር እድገትና ሁለንተናዊ ለውጥ ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና እንዳላቸው የገለፁት የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅ/ቤት ኃላፊና በብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሴቶች ክንፍ የስራ አስፈፃሚ ኮሙቴ አባል ወ/ሮ ለምለም ንጉሴ የሴቶች ክንፍ የፓርቲ ተልዕኮዎችን ከግብ በማሳካት በግንባር ቀደምትነት በመወጣት ጠንካራ ፓርቲ እንዲፈጠር የሴቶች ተሳትፎ አይተኬ ሚና እንደነበረ አስገንዝቧል።

ሴቶች በውሳኔ ሰጪነትና በአመራር ተሳትፎ ላይ ከወረዳ ጀምሮ ያለው ውጤታማነት እጅግ አበረታች መሆኑና ይህ ጠንካራ ተቋም ከግብ እንዲሳካ ማድረግ እንደሚገባ ወ/ሮ ለምለም ተናግሯል።

ባሳለፍነው ሶስት የሩብ ዓመት የበጀት አመት በሴቶች ክንፍ በርካታ መደበኛና ወቅታዊ የንቅናቄ ስራዎች መሠራታቸው የገለፁት በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ባይሳ ፓርቲያችን በሰው ሀይል በፋይናንስ ለማጠናከርና ለመደገፍ የተሰራበት አግባብ እጅግ አመርቂ እንደነበር አስገንዝቧል።

በመጨረሻም የዘጠኝ ወር የስራ አፈፃፀሙ ላይ ውይይት በማድረግና የስራ አስፈፃሚ ኮሙቴዎች በማፅደቅ አቅጣጫ በማስቀመጥ ኮንፈረንሱ ተጠናቋል።

የማዕድ ማጋራት ስራ ለበጎ አላማ በማዋል ህብረ ብሔራዊ እህትማማችነትን ማጎልበት ይገባል!አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያምበብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሴቶች ክንፍ የ2017 ዓ/ም የትንሳኤ...
18/04/2025

የማዕድ ማጋራት ስራ ለበጎ አላማ በማዋል ህብረ ብሔራዊ እህትማማችነትን ማጎልበት ይገባል!
አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያም

በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሴቶች ክንፍ የ2017 ዓ/ም የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት መረሃ-ግብር አደረገ።

የማዕድ ማጋራት ስራ ለበጎ አላማ በማዋል ህብረ ብሔራዊ እህትማማችነትን ማጎልበት ይገባል ያሉት በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያም በዓሉም የሌላቸውን ወገኖቻችን በማካፈል በመረዳዳትና በመተሳሰብ እሳቤ ማክበር እንደሚገባ አስገንዝቧል።

የ2017የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ከ6ሺ 70ዐ በላይ ሴቶች ማዕድ መጋራታቸው የጠቀሱት የክፍለ ከተማው ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ባይሳ በዛሬ እለትም በራስ አቅም ብቻ በጎ ፈቃደኛ ባለሀብቶች በማስተባበር 73 ሴቶ ማዕድ ማጋራቱ ገልጿል።

በማዕድ ማጋራቱ መረሃ-ግብር በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አቶ ተወዳጅ ኃ/ማርያም ፣በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ምክትልና ፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍራኖል ሞሲሳ ፣በብልፅግና ፓርቲ አራዳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ባይሳ ጨምሮ ሌሎች አመራሮች አመራሮች ተገኝቷል።

05/04/2025
በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 2 ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የቤተሰብ የቁጠባ የንቅናቄ መድረክ አካሄደ።አራዳ ወረዳ 02 የብልፅግና ፓርቲ ሚዲያ  ይህ የንቅናቄ መድረክ የሴቶች የተሻለ ተጠቃሚ...
04/04/2025

በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 2 ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የቤተሰብ የቁጠባ የንቅናቄ መድረክ አካሄደ።

አራዳ ወረዳ 02 የብልፅግና ፓርቲ ሚዲያ

ይህ የንቅናቄ መድረክ የሴቶች የተሻለ ተጠቃሚነት እንዲሰፋና ከተረጅነት ልማድ እንዲዎጡ የሚያግዝ ነው ከራስ አልፎ ለቤተሰብ ለሀገር የሚጠቅም ስራ ለመስራትም ትልቅ ሚና ያለው ፕሮግራም ነው።

የወረዳው የሴት ክንፍ ሰብሳቢ ወ/ሪት የኋላሸት ተድላ እንዳሉት ይህ የሴቶች ክንፍ የቤተሰብ የቁጠባ ማስጀመሪያ ነገ ባለትልቅ ራዕይ ያለት ሴት መሆን እንዳለባችሁ እንዲሁም በኢኮኖሚ የተሻለች ሴት፣መስራት መለወጥ እንደምንችል የምናሳይበት ጅማሮ ነው ። ይህ ፕሮግራም በዚህ ብቻ የሚቋጭ አይደለም እናንተ ለሌሎች ሞዴል በመሆን ማስፍትና ውጤታማ መሆን ይጠበቅባችኋል የሚል መልዕክት አስተላልፍለች

በመድረክ ላይ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የአራዳ ክፍለ ከተማ የሴት ክንፍ ሀላፊ ወ/ሮ ገነት ባይሳ እንዳሉት ሴቶች ሁሉንም ማድረግ እንችላለን መቆጠብ ፣መስራት እንደምንችል የምናሳይበት ትልቅ ፕሮግራም ነው ፤ከዚህም ባሻገር ይህ የዛሬው የቁጠባ የንቅናቄ መድረክ በ8ቱም ወረዳ ተግባሩን በማስፍት ጠንካራዋን ሴት መፍጠር እንችላለን ብለዋል ።

የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ሀላፊ አቶ ፀሐዬ ብርሃኑ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ዛሬ የተጀመረው ሴቶች ክንፍ የቤተሰብ ቁጠባ ስርአት ነገ የተሻለ የኢኮኖሚ አውድ መፍጠር እና በርካታ ሴቶችን ከኢኮኖሚ ጥገኝነት ማላቀቅ ይቻላል ዘንድ ትልቅ ተሞክሮ መሆኑን እየገለፅኩ በሌሎች ተግባራትም የወረዳችን ሴት እህቶቻችን የተሻለ ተጠቃሚ እና ግንባር ቀደም ለማድረግ እንደወረዳ የተቻለንን ለማድረግ ዝግጁ ነን ብለዋል ።

በፕሮግራሙ ላይ በአራዳ ክፍለ ከተማ የሴቶች ክንፍ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ገነት ባይሳ፣ አቶ ፀሐዬ ብርሃኑ የወረዳ 02 ብልፅግና ፓርቲ ሀላፊ እንዲሁም ሌሎች የአስተባባሪ አካላትና የሴት ክንፍ ቤተስብ ተገኝዋል

ከተረፈን ሳይሆን ካለን አካፍለን ለተቸገረ መረዳት ሰው የመሆን ትርጉም ነው።           ወ/ሮ ገነት ባይሳየብልጽግና ፓርቲ 5ተኛ ዓመት ምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የአራዳ ክፍለ ከ...
25/11/2024

ከተረፈን ሳይሆን ካለን አካፍለን ለተቸገረ መረዳት ሰው የመሆን ትርጉም ነው።
ወ/ሮ ገነት ባይሳ

የብልጽግና ፓርቲ 5ተኛ ዓመት ምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የአራዳ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ የህሙማን የሚሆን ግብዓት በማቅረብ በጎነት በሆስፒታል መረሃ-ግብር አደረገ።

ከተረፈን ሳይሆን ካለን ለተቸገሩት ለታመሙት መረዳት ሰውኛ ባህሪ ነው ያሉት የክፍለ ከተማው ሴቶች ሊግ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት ባይሳ ይህ የፓርቲያችን ብልጽግና ተልኮ ከሆነው አንዱ የሠው ተኮር ተግባ መረዳዳትና መተሳሰብ ነው፤ ለዚህም የበለጠ ወንድማማችነትና እህትማማችነት የሚያጠናክር ትልቅ ተግባር ነው ብሏል።

ይህ መረሃ ግብር የፓርቲያችን ምስረታ በዓል ምክንያት ተደርጎ በክፍለ ከተማው ሴቶች ሊግ የተደረገና በቀጣይም በሌላ ተግባራቶች እንደሚቀጥል ወ/ገነት አሳስቧል።

በጎነት ከውስጥ የሚመነጭ ውስጣዊ አዎንታዊ እርካታ የምናገኝበት ነው ያሉት የክፍለ ከተማው የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ እንደዚህ አይነት በጎ ተግባራቶች አጠናክረን በመቀጠል የፓርቲያችን ብልጽግና ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ግብ ከግብ ማድረስ ይገባል ብሏል።

የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arada sub city woreda 2 womens lig/አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ሴቶች ሊግ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category