08/06/2026
የመንግስትን እና የፓርተውን ተግባር በብቃት በመወጣት ከወረዳ ወደ ዞን ማዕከል በሹመት ለወጡ የሥራ ኃላፊዎች ሽኝት ተደረገላቸው።
የኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ መንግስት በክብር ከወረዳ አመራርነት ወደ ዞን አመራርነት ለተቀላቀሉ አመራሮች የሽኝት መርሃ ግብር አካሂደዋል።
የቀድሞ የአመያ ዙሪያ ወረዳ ም/አስ/ሪና የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢዮብ ስለሽ እና የወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ማሬ በቀለ የክብር አሸናኘት ተደርጓላቸዋል።
በሽኝት መርሃ ግብር ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ዋና አስ/ር አቶ ወንድማገኝ ኡቴ ጠንካራ አመራር ሆነው መንግስትንና ሕዝብን በትጋት በማገልገል በተግባር ውጤታቸው ወደ ዞን አመራር ሆነው በመሄዳቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው መልካም የሥራ ጊዜ እንድሆንላቸውም ተመኝተዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የዞኑ ም/አስ/ሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ወጁ ሽኝት የተደረገላቸው አመራሮች በወረዳው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህዝቡን በቀናነት ሲያገለግሉ በመቆየታቸው ምስጋና በማቅረብ በቀጣይም መንግስት አምኖ የሰጣቸውን አደራ በበለጠ ትጋት ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በመጨረሻም በክብር ለተሸኙ አመራሮች የወረዳው አስተዳደር ስጦታ በማበርከት የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።
በመድረኩም የዞኑ ም/አስ/ሪና የገብዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ወጁ ፣ የወረዳው ዋና አስ/ር አቶ ወንድማገኝ ኡቴ ፣ የወረዳው ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አሻግሬ አለማየሁ፣የዞኑ ደጋፊ አመራሮች፣ የወረዳው ስራ አስፈፃሚዎች እና ፑል አመራሮች በተገኙበት የሽኝት ሥነ-ስርዓት ተደርጓል።