Arada Woreda 5 Communication

Arada Woreda 5 Communication to discribe the governement

"እምርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ታላቅ የንግድ ኤግዚብሽንና ባዛር ተከፈተ።ነሀሴ 30/2017 ዓ.ምአራዳ ወረዳ 5 ኮሙኒኬሽን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ፒያሳ አካባቢ  "እምርታ ለ...
05/09/2025

"እምርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ታላቅ የንግድ ኤግዚብሽንና ባዛር ተከፈተ።

ነሀሴ 30/2017 ዓ.ም
አራዳ ወረዳ 5 ኮሙኒኬሽን

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ፒያሳ አካባቢ "እምርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በተከፈተው ታላቅ የንግድ ኤግዚብሽንና ባዛር ላይ ወ/ሮ ሽታየ መሀመድ የአዲስ አበባ ከተማ ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ አቶ መስፍን አሰፋ የአዲስ አበባ ንግድ ድርጅት ሀላፊን ጨምሮ የከተማ ፣ የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ በመክፈቻ ዝግጅቱ ላይ እንደተናገሩት በአሉን ያለምንም ችግር ለማክበርና ዘላቂ የተረጋጋ የግብይት ስርአት እንዲኖር የከተማ አስተዳደሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸው በዛሬው እለት እስከ ጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም የሚቆዩ በከተማ ደረጃ 20 ታላላቅ ባዛሮች መከፈታቸውንና ቀደም ሲል አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ከ219 በላይ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በታላቅ ቅናሽ አገልግሎት የሚሰጡ በመሆኑ ህብረተሰቡ ተረጋግቶ ግብይት እንዲፈጽም መልእክት አስተላልፈዋል።

ወ/ሮ ሀቢባ አክለውም የዋጋ ጭማሪ ሲያጋጥም ነዋሪው በአቅራቢያው ለሚገኙ ንግድ ጽ/ቤቶች ጥቆማ በመስጠት አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪን በመከላከል ረገድ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት አሳስበዋል።

የአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጌታሁን አበራ በበኩላቸው በባዛሩ ላይ ለበአሉ ግብአት የሚሆኑ የግብርና ምርቶች፣ የእንስሳት ተዋጽኦ፣ የኢንዱስትሪ ምርቶችና አልባሳት በብዛትና በጥራት መቅረባቸውን ገልጸው ፍትሃዊ ግብይት እንዲኖር አስተዳደሩ ባዛሮችን በማዘጋጀትና የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን በማጠናከር በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

05/09/2025
“በዕውቀት እና ክህሎት የበቃ ትውልድ በማፍራት ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋታለን” በሚል መሪ ሀሳብ 32ኛው የትምህርት ጉባኤ ተካሄደ፡፡አራዳ ነሐሴ 30/2017 ዓ.ምየአራዳ ክፍለ...
05/09/2025

“በዕውቀት እና ክህሎት የበቃ ትውልድ በማፍራት ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋታለን” በሚል መሪ ሀሳብ 32ኛው የትምህርት ጉባኤ ተካሄደ፡፡

አራዳ ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም

የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት 32ኛውን የትምህርት ጉባኤ “በዕውቀት እና ክህሎት የበቃ ትውልድ በማፍራት ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋታለን” በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው እለት አካሂዷል፡፡

የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታሁን አበራና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናዖል ጫላን ጨምሮ የትምህርት አመራሮች፣ የዘርፉ ያሉ ሰራተኞች፣ መምህራንና ተሸላሚ ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በጉባዔው ተሳትፈዋል፡፡

የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታሁን አበራ በመክፈቻ ንግግራቸው መንግስት ኢትዮጵያን ታላቅና ገናና ለማድረግ በትምህርትና ክህሎት የበቃ ትውልድ መፍጠር ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ባለራዕይ ህዝብ እንዲፈጠር እየሰራ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ለአንድ አገር እድገት ትምህርት ወሳኝ ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው ወንድማማችነትና እህትማማችነት እንዲፀና፣ ልማትና ሁሉን አቀፍ ዕድገት እንዲመጣም የሚያስችል በመሆኑ ትምህርት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በክፍለ ከተማው ያሉ ባለድርሻ አካላት የትምህርት ዘርፍ ስራዎችን በማጠናከርና በማዘመን ሂደት ያላቸውን አስተዋፅኦ አጠናክረው በመቀጠል አገሪቱ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን በሚደረገው ርብርብ የድርሻቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናዖል ጫላ እንደጠቆሙት መንግስት ትምህርት ላይ ልዩ ትኩረት በማድረጉ የተማሪ ስነ-ምግባርና ውጤት እየተሻሻለ ነው ብለዋል፡፡

በ2017 ዓ.ም ትምህርት ቤቶች ስርዓተ ትምህርቱን ሪፎርም በማድረግ፣ አዕምሮን የሚያጎለብት የስፖርት መርኃ-ግብሮችን በማከናወን፣ ተማሪዎች ትምህርት ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ የተማሪዎች ምገባ፣ የተማሪዎች ጤናን መጠበቅ፣ ሰርቶ ማሳያ የትምህርት ቤቶች የከተማ ግብርናና የተማሪዎች ቴክኖሎጂ እውቀት ግንባታ ላይ ትኩረት ተደርጎ የተሰራ መሆኑን ገልፀው ሁሉም ባለድርሻ ይህን እንዲያጠናክር ምክትል ቢሮ ኃላፊው አሳስበዋል፡፡

በ2017 የትምህርት ዘመን በትምህርት ለትውልድ ህብረተሰቡን ያሳተፈ ንቅናቄ በማድረግ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ በገንዘብ የሚተመን የትምህርት ቤቶች አንኳር ችግሮች መፈታት መቻሉን የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዱጋሳ ፍቃዱ ገልፀዋል፡፡

በጉባዔው የ2017 የትምህርት ዘመን አፈፃፀም የቀረበ ሲሆን የከተማ አቀፍና አገር አቀፍ ፈተናዎች ያለምንም እንከን መሰጠታቸው፣ የቀዳማይ ልጅነት ተግባራዊነት፣ የልዩ ፍላጎትና የጎልማሶች ትምህርና ፈተና አሰጣጥ ውጤታማ መሆን መቻሉ ተመላክቷል፡፡

በ2017 የትምህርት መንፈቅ የነበሩ ጥንካሬዎችን ለማጠናከርና ማነቆዎችን በጋራ ርብርብ ለመፍታት በተለይም በ2018 ዓ.ም የተማሪዎችን ውጤት የበለጠ ለማሻሻል ግብዓት የሚሆኑ ሃሳብ አስተያየቶች ተነስተው ምላሽ ተሰጥቷል፡፡

በመጨረሻም 2017 የትምህርት ዘመን ውጤታማ የሆኑ የትምህርት ቤተሰብ እና የደገፉ ባለድርሻ አካላት የዕውቅናና ሽልማት ተበርክቶ በ2018 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ውጤታማ ለመሆን የጽ/ቤቱ የአቋም መግለጫ ወጥቶ ተጠናቋል፡፡

05/09/2025
05/09/2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arada Woreda 5 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category