Haadha Keol ni jaallanna.

Haadha Keol ni jaallanna. Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Haadha Keol ni jaallanna., Grocers, Lafto, Addis Ababa.

15/12/2025

ሀገር ተረካቢ ትውልድ በመገንባት ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን እናረጋግጣለን!!

ተተኪው ትውልድ በአካል ዳብሮ ፣ በምግባር ተቀረፆ ፣ በእውቀት ተሞልቶ እንዲያድግ የሚደረገው ርብርብ የፓርቲያችን እና የመንግስታችን ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ልዩ የትኩረት አቅጣጫ ነው።

ለዛሬው እና ለነገውም ትውልድ በልዩ ትኩረት የሚተጋው ፓርቲያችን የኢትዮጵያን መሰረት ለማፅናት የነገውን ሀገር ተረካቢ ትውልድ እየገነባ ይገኛል።

ፓርቲያችን ትውልድ ለመገንባት ዘርፈ ብዙ ስራዎች አቅዶ እየሰራ ሲሆን ለአብነትም በከተማችን የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ጨምሮ ለህፃናት ፣ ለታዳጊዎች እንዲሁም ለወጣቶች ዘላቂ ተጠቃሚነት ብርቱ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን መጥቀስ ይቻላል።

የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራማችንም ተማሪዎች ብቻም ሳይሆኑ ወላጆችም ለልጆቻቸው ምግብ እንዲሁም ለትምህርት ቁሳቁሳቸው ተጨንቀው ከትምህርት ገበታቸው እንዳያርቋቸው ተግባራዊ ምላሽ ሰጥቷል።

የትምህርት ጥራትን ለማሳደግም ከፍተኛ አስተዋፅፆ እንዳለውም ከተገኘው አበረታች ለውጥ ማየት ተችሏል።

የትምህርት ቤት ምገባ መርሀ ግብር በመጠነ ማቋረጥን በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ሲሆን ፣ የተማሪዎችን የመማር ብቃት እና የትምህርት ትኩረትም ከፍ አድርጓል።

ለህፃናት መዋያዎች እና ለህፃናት መጫዎቻዎች የከተማ አስተዳደሩ የሰጠው ትኩረትም ከተማችንንም ተመራጭ እያደረገ በመሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም።

እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ከተማችን ለቅድመ መደበኛ ትምህርት መስፋፋት እንዲሁም ጥራት የሚደረገው ጥረትም የትውልድ ግንባታ ጉዟችንን ተስፋ የሚጣልበት አድርጎታል።

በየአካባቢው እየተገነቡ የሚገኙ የታዳጊዎች እና የወጣቶች የስዕብና መገንቢያ እና የስፖርት ማዘውተሪያዎችም በስነ ምግባር የተመሰገን ፣ በአካል የዳበረ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመገንባት ፓርቲያችን ያስቀመጠው ግልፅ አቅጣጫ ውጤት ነው።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

15/12/2025
04/11/2025

🚨 *ጄነራል ማሾ ለጄነራል ሳሞራ የኑስ መልስ ሰጡ ‼️*

📌ሜጀር ጀነራል ማሾ በየነ በሰጡት ምላሽ ጀነራል ሳሞራ በቅርቡ በተካሄደው የትግራይ ጦርነት ወቅት ህዝቡ ጥቃት ሲደርስበት ሊከላከልለት ፈቃደኛ ባለመሆንና ምላሽ ባለመስጠት የትግራይን ህዝብ የካዱ እንዲሁም በጦርነቱ ወቅት ከአብይ አህመድ ጋር ይገናኙ የነበሩ ሰው ናቸው ሲሉ ክፉኛ ወቅሰዋቸዋል።

📍በተጨማሪም ጀነራል ሳሞራ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አስመራን ባለመያዝ ዙሪያ እነ መለስ ዜናዊን መወቀሳቸው ስህተት መሆኑን የገለጹት ጀነራል ማሾ ውሳኔው ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ ማዕቀብ ለመታደግ በወቅቱ የነበሩ ፖለቲከኞችና ጀነራሎች (ሳሞራን ጨምሮ) በጋራ የወሰኑት ውሳኔ እንደነበር አስረድተዋል በመሆኑም ሳሞራ እራሳቸው የውሳኔው አካል ሆነው ሳለ አሁን ጻድቅ መስለው በህይወት በሌሉ የትግል ጓዶች ላይ ማላከክ እንደሌለባቸውና ለስህተቶች በጋራ መጠየቅ እንዳለባቸው በመግለጽ ኮንነዋቸዋል።

Address

Lafto
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haadha Keol ni jaallanna. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category