05/11/2025
የአርሲው የ4 ዓመቱ ህጻን ቀኝ እግሩ ተቆ*ረ*ጠ!!😭💔
: ከአርሲ ጥቃት ተርፎ ከእናቱ አ*ስ*ክ*ሬ*ን የተነሳው ያ ለመከራ የተጠራው ብላቴና ቋንጃው ላይ በተተኮሰ ጥይት ምክንያት አንድ እግሩ የተጎዳው የ4 ዓመቱ ህጻን እጅግ በጣም አድካሚ ከሆነ የሀኪሞች ርብርብ እና ልፋት በኃላ እግሩን ማዳን አልተቻለም ።
የአራት ዓመቱ ሕፃን ታምራት አውግቸው፣ በጥይት የተመታና የተመረዘው ቀኝ እግሩ ተቆርጦ መውጣቱ ተሰምቷል ።
ሕፃኑ ታምራት አውግቸው በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚገኘው ክርስቲያን ሆስፒታል ውስጥ ሲታከም ቆይቷል።
የሆስፒታሉ ሐኪሞች እግሩ ሳይቆረጥ ለማዳን የሚያስፈልጉትን ሕክምናዎች ሁሉ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም፣ ሙከራው አልተሳካም።ሕፃኑ የደረሰበት ጉዳት ከባድ ከመሆኑም በላይ፣ ሕመሙ ለሕይወቱ አስጊ እየሆነ በመምጣቱ ምክንያት፣ እግሩን ለመቁረጥ መወሰኑን ምንጮች አስታውቀዋል።
ሕፃኑ ታምራት አውግቸው ቀኝ እግሩ የተቆረጠው ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ይህ የአንድ እግር መቆረጥ ርዕስ ብቻ አይደለም። ጠላት ምን ያህል ተስፋ እና መኖራችንን ለመቁረጥ የመጣበትን ጨካኝነት የተመለከትንበት የሁላችንም ህመም ነው ። እንግዲህ አንተ ብላቴና ፈጣሪ ይርዳህ!!😭💔