South Ethiopia Transport and Road bureau

South Ethiopia Transport and Road bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from South Ethiopia Transport and Road bureau, Grocers, South, Dila.

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ያይቄ ቀበሌ እያስገነባ ያለው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንደሚጠናቀቅ ገለጸ‎ዲላ ነሐሴ 28/...
03/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ያይቄ ቀበሌ እያስገነባ ያለው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንደሚጠናቀቅ ገለጸ

ዲላ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

‎ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ያይቄ ቀበሌ “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል በክረምት በጎ ፈቃድ እያስገነባ ያለው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንደሚጠናቀቅ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት ቢሮ ም/ኃላፊ ዶ/ር ብርሃኑ ገቦ ገልጿል።

‎የቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ብርሃኑ ገቦ እንደገለጹት፣ የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቱ በአራት ዋና ዋና የሥራ መስኮች እየተከናወነ ይገኛል።

‎እነዚህም ሰው ተኮር ተግባራት፣ የመንገድ ደህንነት፣ መሠረተ ልማት እና ችግኝ ተከላ ሲሆኑ፣ በሰው ተኮር ተግባራት የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የማዕድ ማጋራትና የትምህርት ቤት ቁሳቁስ ድጋፍ እየተደረገ እንዳለ ተናግሯል።

‎በመንገድ ደህንነት ዘርፍ የእግረኞች መሻገሪያ ዜብራ መቀባት፣ የተሽከርካሪዎች ቴክኒክ ፍተሻ ማከናወን፣ የትራፊክ ሕግና የመንገድ አጠቃቀም ግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ በማለት ገልጿል።

‎በመሠረተ ልማት ዘርፍም የመንገድና የድልድይ ጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ ሲሆን፣ በአካባቢ ጥበቃና በዘላቂ ልማት ላይ ያተኮረ የችግኝ ተከላም በተጨማሪ እየተከናወነ መሆኑን ተገልጿል።

‎በያይቄ ቀበሌ እየተገነባ ያለው የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ግንባታም አሁን ወደ መጠናቀቂያ ደረጃ ደርሷል። ለቤቱ የተሟላ የቤት ዕቃ ከማሟላት በተጨማሪ ሶስት ፍየሎች የሚሰጡ ሲሆን፣ በቤቱ ዙሪያ ለምግብነት የሚውሉ ሀለኮ፣ ማንጎና አቮካዶ ችግኞችም ተተክለዋል።

‎ይህም የበጎ ፈቃድ ተግባሩ መኖሪያ ቤት ብቻ በመገንባት የማይወሰን ሆኖ፣ ቤተሰቡ በቀጣይ ዘላቂ የኑሮ መሠረት እንዲኖረው የሚያግዙ ተጨማሪ ድጋፎችንም ያካተተ መሆኑን ተናግሯል።

‎የቤቱ ግንባታ በቀጣይ ሳምንት ተጠናቆ በክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።

በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገለጸዲላ፦ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት አ...
01/09/2026

በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገለጸ

ዲላ፦ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በቀጣይ 2019 ዕቅድ ዙሪያ በትራፊክ አደጋ መከላከልና በሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ የግምገማ መድረክ በዲላ ከተማ አካሂዷል።

መድረኩን የመሩት የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር ብሩ ማርቆስ፣ የትራፊክ አደጋን የመቀነስ ኃላፊነት የተወሰኑ አካላት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋ ሊሆን ይገባል ብለው የትራፊክ ፖሊስ አደጋውን ለመቀነስ ሁሉም አካላት በሚሠሩት ሥራ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

አዛዡ አክለውም፣ የአደጋውን ስፋትና አሳሳቢነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ ከሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር በቅንጅት የመሥራት ጉዳይ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል።

ይህንን ለመከላከል በጋራ ጥረት እየተሠራ መሆኑን የመምሪያው የትራፊክ አደጋ መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ዳንኤል በደቻ ተናግረዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ከተለያዩ አካላት ጋር በጋራ በተሠሩ ሥራዎች አበረታች ለውጥ መመዝገቡን ምክትል ኢንስፔክተሩ ገልጸዋል።

በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ አሽከርካሪዎች ባልተፈቀደ ቦታ መቆም፣ ያለመንጃ ፈቃድና ያለ ታርጋ ማሽከርከር፣ እንዲሁም የአደጋ ጊዜ መከላከያ ጭንብል ሳይጠቀሙ ማሽከርከር የተከለከለ መሆኑን የማስጠንቀቅ ሥራዎች ሲሠሩ መቆየታቸውን ምክትል ኢንስፔክተር ዳንኤል አመላክተዋል።

በሰውና በንብረት ላይ አደጋ እንዳይደርስ የቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም አስመዝግበው የማበረታቻ ሽልማት ካገኙት መካከል ምክትል ኢንስፔክተር ዳዊት ደግፌ እና ኢንስፔክተር መምህሩ አየለ ይገኙበታል። ተሸላሚዎቹ በተሰጣቸው ሽልማት ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፣ በቀጣይ ከዚህ በተሻለ ለመሥራት እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል።

የትራፊክ አደጋንና ወንጀልን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የኅብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ፣ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ተጠይቋል።

ዘገባው ጌዴኦ ቴሌቪዥን

የመንገድ መሠረተ ልማት ሥራዎች ለሀገር እድገት ወሳኝ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በደቡብ ኦሞ ዞን የማሌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩለበርካታ ዓመታት ወረዳዉን ከዞን ማእከልና ቀበሌን...
29/08/2026

የመንገድ መሠረተ ልማት ሥራዎች ለሀገር እድገት ወሳኝ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በደቡብ ኦሞ ዞን የማሌ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

ለበርካታ ዓመታት ወረዳዉን ከዞን ማእከልና ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኝ መንገድ እና የኮይቤ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጋር የሚያገናኝ መንገድ ችግርን መቅረፍ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ መሆኑን ነዉ ነዋሪዎች የሚያነሱት፡፡

አስተያየታቸውን ከሰጡት የወረዳው ነዋሪዎች መከላከል አቶ ግዛዉ ግምጃ ለማ ሱሜ መልካሙ ቱራዣ እና ወይዘሮ ዘማነሽ ሥረጋ በጋራ እንደገለፁት፤ አሁን ላይ በልዩ ሁኔታ በሁሉም የወረዳው ክላስተሮች እየተካሄዱ የሚገኙ የመንገድና የድልድይ ስራዎች ለበርካታ አመታት ምላሽ ያላገኙ የህዝቡን ጥያቄዎች እየመለሰ የሚገኝ አስደሳች ተግባር ነው።

በ2018 ዓ.ም ግንቦት ወር በተካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በማሌ ወረዳ ተፎካካሪ ከነበሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በኢትዮጵያ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲን በመወከል የተወዳደሩት አቶ ብርሃኑ ዳሞ በበኩላቸው፤ የመንገዱ ስራ አሁን በሚታየዉ ልክ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ወደ ተግባር መገባቱ የህብረተሰቡ አንገብጋቢ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች እየተመለሱ በመሆናቸዉ ደስታ የተሰማቸው መሆኑን ተናግረዋል።

የማሌ ወረዳ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አማር ባርጩማ በበኩላቸዉ፤ የወረዳው ህዝብ ከሚያነሳቸው የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች መካከል የመንገድ መሠረተ ልማት ቀዳሚ እንደነበር እና በአሁኑ ሰዓት በአጭር ጊዜ ወደ 54 ኪሎ ሜትር የሚሆን የመንገድ ስራ በተለያዩ የመንገድ ሥራ በፌደራልና በክልል መንግሥት እንዲሁም በህብርተሰቡ ተሳትፎ በተፋጠነ መልኩ እየተከናወኑ እንደሆነ አብራርተዋል።

የተጀመረዉ የመንገድ ስራ ሲጠናቀቅ ህብርተሰቡ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል በወረዳው ማዕከል እና ኮይቤ ቀበሌ መናኸሪያ እያዘጋጀ እንደሚገኝ ሀላፊዉ አያይዘው አሰረድተዋል።

የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ እንደገለፁት፤ ወረዳዉ ሰፋ ያለ የመንገድ ችግረ የነበረበትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየ መሆኑን ጠቁመዋል።

አያይዘዉም ወረዳዉ ለክልሉ ባቀረበዉ ጥያቄ መሠረት ክልሉም ፈጣን ምላሽ በመስጠት የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮጀክት RcAFs እንዲታቀፋ በማድረግ የመንገድ ተደራሽነትን በዘላቂነት ሊፈታ በሚችል መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝ አስርድተዋል።

ዘጋቢ፡ ዳኛቸው ደሴ - ከጂንካ ጣቢያችን

በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ-ውሳሞ-ፃይቴ-ማዞዶይሳ 19.6 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ስራ ጉብኝት ተካሄደነሐሴ 22/2018 ዲላበጉብኝቱ የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ...
27/08/2026

በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ-ውሳሞ-ፃይቴ-ማዞዶይሳ 19.6 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ስራ ጉብኝት ተካሄደ

ነሐሴ 22/2018 ዲላ

በጉብኝቱ የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ እንደገለፁት ለመንገዱ ስራ የክልሉ መንግስት ልዩ ትኩረት በመስጠት ትልቅ ስራ ተሰርቷል ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ምንም አይነት መኪና የማይገባበት አከባቢ በመሆኑ ከዚህ ቀደም በነበረው የመሬት ናዳ የመንገድ አለመኖር ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሎ እንደነበረ ገልፀው ኮንትራክተሩ በፍጥነት መጨረስ ያስፈልጋል ብለዋል።

የመንገዱ ስራ አደጋው ከደረሰ ጀምሮ እየተሰራ ያለ ቢሆንም ኮንትራክተሩ ስራውን አድምቶ ሰርቶ በአጭር ጊዜ እንዲያጠናቀቅ ወረዳ ዞን እና አርባምንጭ ዲስትሪክት በቅንጅት ሰርተው ማጠናቀቅ ያስፈልጋል ብለዋል።

ስራው በጥሩ ደረጃ ያለ ቢሆንም እንደ ቢሮአችን ስራው በሚፈለገው ፍጥነት እየተሰራ አይደለም ብለው አከባቢው ዝናባማ በመሆኑ ፍጥነት መታከል እንዳለበት ገልፀዋል።

የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ ኢርኮ እንደገለፁት መንገዱ ክረምት ከመግባቱ በፊት ፈጥኖ መጨረስ ያስፈልጋል ብለዋል።

መንገዱ ለአከባቢው ማህበረሰብ የሚሰጠው ጠቄሜታ ከፍተኛ በመሆኑ መንገዱ በሚፈለገው ፍጥነት እየተሰራ ባለመሆኑ ከዚህ በላይ መፍጠን ያስፈልጋል ብለዋል።

የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ስራና ክህልት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀኪሜ አየለ እንደገለፁት መንገዱን ውሎ አድሮ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የወረዳው አስተዳደር አካላት ከዚህ በላይ የሆነ የልማት ስራ ስለሌለ ሁሉንም አቅም አሟጦ በመጠቀም ስራውን በየወቅቱ በመገምገም ማስጨረስ ያስፈልጋል ብለዋል።

የአርባምንጭ ድስትሪክትም በዚሁ ልክ ለመንገዱ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል አሁን ያለውን እድል በአግባቡ በመጠቀም ስራውን በሁለት ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ለማጠናቀቅ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በጉብኝቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ ኢርኮ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ምክትል ኃላፊዎችና የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል ።

ዘገባው የቢሮው ኮሚኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ አራት ወረዳዎችን የሚያገናኝ የ48 ኪ.ሜ መንገድ ስራ በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ተጀመረነሐሴ 21/2018 ዲላበደቡብ ኢትዮጵያ መን...
27/08/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ አራት ወረዳዎችን የሚያገናኝ የ48 ኪ.ሜ መንገድ ስራ በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ተጀመረ

ነሐሴ 21/2018 ዲላ

በደቡብ ኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በጋሞ ዞን የሚገነባው መንገድ ቆላ ሻራ ሱሌ ሳንጋ 48 ኪ.ሜ መንገድ ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ

በማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ እንደገለፁት መንገዱ የረጅም አመት የህዝብ ጥያቄ እንደነበረ ገልፀዋል።

መንገድ ለሰው ልጅ ደምስር እንደሚያስፈልገው ሁሉ መንገድ ለማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር እንደ ደምስር የሚያገለግል ዋነኛ መሳሪያ ነው ብለዋል።

በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ከ18 በላይ ፕሮጀክቶች አልቋል ይህም ከ360 ኪ.ሜ በላይ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል አጠቃላይ በክልሉ መንግስት 40 ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለትራፊክ ክፍት ሆነዋል ብለዋል።

በአከባቢው የሚመረቱ ምርቶችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብና አራት ወረዳዎችን የሚያስተሳስር ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው ከ48 ኪ.ሜ በላይ የሚረዝም የአርሶአደሩን ህይወት የሚቀይር መንገድ ዛሬ አስጀምረናል ብለዋል።

መንገዱ በሚያልፍበት አከባቢ ሁሉ ህብረተሰቡ አጥር ቤት ዛፍ በማንሳት መተባበር ያስፈልጋል ብለው በተለይ ክልሉ መንገዶች ባለስልጣን መንገዱን በጥራት በፍጥነት ጨርሶ እንደሚያስረክብ ትልቅ እምነት አለኝ ብለዋል።

የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳደርና ስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀኪሜ አየለ መንገድ የልማት ሁሉ መሰረት ነው ለትምህርት ለጤና ለግብርና ስራ ግብአት ማቅረቢያ መንገድ ዋና መሳሪያ ነው ብለዋል።

አከባቢው በልማት በጣም የተጠማና በከፍተኛ ሰንሰለታማ ተራሮች መከበቡ አስቸጋሪ አድርጎ ቆይቷል ብለው የሚሰራው መንገድ አራት መዋቅር የሚያገናኝ ሲሆን ዲታ፣ ጋጮ ባባ ፣ጬንቻ ፣አርባምንጭ ዙሪያ አራት ወረዳዎችን የሚያገናኝ ነው ብለዋል።

በመንገዱ ስራ ህብረተሰቡ ወሰን ከማስከበር አንፃር መተባበር ያስፈልጋል ብለዋል እንዲሁም መንገዱን መጠበቅና በመንከባከብ ረጅም እድሜ እንዲቆይ ያስፈልጋል ብለዋል።

በማስጀመሪያ መርሃግብር የቢሮው ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ ኢርኮ የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ (ዶክተር) የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሀኪሜ አየለ የክልል የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

ዘገባው የክልሉ ቢሮ ኮሚኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

27/08/2026

፣በድልድይ፣በትራንስፖርት ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በከፊል

በጋሞ ዞን ሰላምበር-ዛዳ-ጨንቻ -አርባምንጭ አዲስ የትራንስፖርት ስምሪት መስመር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ አስጀመረነሐሴ 20/2018 ዲላ በጋሞ ዞን...
26/08/2026

በጋሞ ዞን ሰላምበር-ዛዳ-ጨንቻ -አርባምንጭ አዲስ የትራንስፖርት ስምሪት መስመር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ አስጀመረ

ነሐሴ 20/2018 ዲላ

በጋሞ ዞን ሰላምበር ከተማን ከአርባምንጭ ከተማ ጋር የሚያገናኝ አዲስ የትራንስፖርት መስመር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶክተር) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ(ዶክተር) አስጀምረዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት ብርሃኑ ጌቦ(ዶክተር) ዛሬ በይፋ ሰላምበር-ዛዳ-ጨንቻ-አርባምንጭ ከተማን የሚያገናኝ ሲሆን መንገዱ የህዝቦችን መስተጋብር የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

መንገዱ ሰላም በር -ዛዳ-ጨንቻ-አርባምንጭ ከተማ ህዝቦችን የሚያስተሳስር ነው ብለው መንገዱ በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነው ብለዋል።

የታሪፍ ሁኔታው በገጠር መንገዶች በተቀመጠ መስፈርት መነሻ ተመን ወጥቶ ከነገ ጀምሮ የትራንስፖርት ሲስተሙ በይፋ መጀመሩን የቢሮው ምከትል ኃላፊና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ(ዶክተር) ገልፀዋል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ እንደገለፁት 6 አዲስ የስምሪት መስመር መከፈቱና ከዚህ ቀደም ከነበረው የጉዞ ርቅት ሰላምበር -ወላይታ ሶዶ - አርባምንጭ እና ዋጫ-ወላይታ ሶዶ-አርባምንጭ ጉዞን በ106 ኪ.ሜ የቀነሰ መሆኑን ገልፀዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶክተር) የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ ኢርኮ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ጌቦ (ዶክተር) የክልሉ የጋሞና የቁጫ ወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

ዘገባው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳና የቁጫ አልፋ ወረዳን የሚያገናኝ በሌማሴ ወንዝ ላይ የሚገነባ ድልድይ በክልልና በዞን ከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት ተካሄዷል ነሐሴ 20/2018 ዲላበ...
26/08/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በቁጫ ወረዳና የቁጫ አልፋ ወረዳን የሚያገናኝ በሌማሴ ወንዝ ላይ የሚገነባ ድልድይ በክልልና በዞን ከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት ተካሄዷል

ነሐሴ 20/2018 ዲላ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን በጋሞ ዞን የቁጫ ወረዳና የቁጫ አልፋ ወረዳን የሚያገናኝ በሌማሴ ወንዝ ላይ የሚገነባ ድልድይ ግንባታ በክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶክተር) የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ እርኮና ሌሎች ከፍተኛ የክልልና የዞን አመራሮች በጉብኝቱ ተገኝተዋል።

በምልከታው ወቅት ንግግር ያደረጉት ቢሮው ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ እንደገለፁት በተቀመጠው ዕቅድ መነሻ ለማጠናቀቅ ከዚህ በላይ ፍጥነት ያስፈልጋል ብለዋል።

የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር እድሬ ኢርኮ እንደገለፁት ስራውን ፍጥነትና በጥራት ለማጠናቀቅ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶክተር ) እንደገለፁት ድልድዩ ለህዝቡ የሚሰጠው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ ተቋራጩ በልዩ ትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

ክርስቲያን ጠቅላላ ተቋራጭ ግንባታው እየተሰራ ያለ ሲሆን በተቀመጠው ውል መነሻ ለማጠናቀቅ የተሰጡ አስተያየቶችን ለመተግበር ቃል ገብተዋል።

ዘገባው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን 16 ሜትር ርዝመት ያለው ድልድይ ግንባታ የዞንና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀመረከዛዳ-ሰላ...
26/08/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን 16 ሜትር ርዝመት ያለው ድልድይ ግንባታ የዞንና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀመረ

ከዛዳ-ሰላምበር 21.5 ኪ.ሜ መንገድ ላይ በሚገኝ ሹመቴ ወንዝ ላይ የሚገነባ ድልድይ ማስጀመሪያ መርሃግብር የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተስፋዬ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ(ዶክተር) የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ኢንጂነር እድሬ ኢርኮ በጋራ አስጀምረዋል ።

በሳምሶን ደገፉ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ስራው የሚከናወን ሲሆን እሰከ ጥቅምት 30/2019 ስራውን ለማጠናቀቅ ውል ተገብቷል።

ከዛላ-ሰላምበር 21.5 ኪ.ሜ መንገድ ላይ ከሚኘኙ ድልድዮች አራቱ የተጠናቀቀ ሲሆን 5ኛው ሹመቴ ወንዝ ላይ የሚገነባው ድልድይ ስራው በይፋ ተጀምሯል ።

ዘገባው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

Address

South
Dila

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Transport and Road bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category