Aysha ahmed

Aysha ahmed Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Aysha ahmed, Grocers, Dire Dawa.

04/06/2026
04/06/2026
04/06/2026
04/06/2026
03/06/2026

ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መርጣለች!

ሀገራችን ባከናወነችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረዣዥም የመራጮች ሰልፍ መስተዋሉ፣ ዜጎች በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ስለመሆናቸው ጉልህ ማሳያ ነው።

የዕድሜ መግፋት ፣ የጤና ሁኔታ መታወክ፣ አራስነት፣ ከቤት መቆየትን የግድ ያለው አሰገዳጅ ክስተት ሳይበግራቸው ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ይበጀኛል ያሉትን መርጠዋል።

አንድ ድምፅ ዋጋ እንዳለው በመረዳት ከሌሊት እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

በምርጫው ዕለት የታዩ ረዣዥም የመራጮች ሰልፎች የሕዝብ የፖለቲካ ፍላጎት እና የዴሞክራሲ ተሳትፎ መጉላትን የሚያሳዩ ናቸው።

03/06/2026

በሐረሪ ክልል 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ ነው

በሐረሪ ክልል በበልግ እና መኸር እርሻ በድምሩ 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ሮዛ ኡመር እንደገለፁት፦በክልሉ ያለውን አነስተኛ መሬት በአግባቡ ተጠቅሞ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

በክልሉ በ2018/19 በበልግ እና መኸር እርሻ በድምሩ 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በበልግ ዝናብ እስካሁን 8 ሺህ 681 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ጠቁመው፥ ቀሪው 3 ሺህ 275 ሄክታር በክረምት መኽር ዝናብ ቶሎ ደራሽ ማሽላ እና ስንዴ ለመዝራት አሰፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ሶስት የገጠር ወረዳዎች በሚገኙ ማሳዎች ላይ እየለሙ የሚገኙት ሰብሎችም ማሽላ፣ በቆሎ እና ስንዴ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ለመኸር እርሻው ምርትና ምርታማነት ማደግ አስፈላጊው የማዳበሪያ፣ የዘርና ሌሎች የግብርና ግብዓት አቅርቦት ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ያመለከቱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ በምርት ዘመኑ እየለሙ ካሉ ሰብሎች 300 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰበሰብ መታቀዱንም አስረድተዋል።

በየደረጃው ያሉ የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ አስፈላጊውን ሙያዊ እገዛና ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም አርሶ አደሩን ከዝናብ ጠባቂነት ከማላቀቅና ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃር አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።

በቀጣይም የተገኙ አበረታች ውጤቶችን በማስቀጠል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበትና ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ የላቀ ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

03/06/2026

በሐረሪ ክልል 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በበልግ እና መኸር እርሻ በድምሩ 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ሮዛ ኡመር እንደገለፁት፦በክልሉ ያለውን አነስተኛ መሬት በአግባቡ ተጠቅሞ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

በክልሉ በ2018/19 በበልግ እና መኸር እርሻ በድምሩ 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በበልግ ዝናብ እስካሁን 8 ሺህ 681 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ጠቁመው፥ ቀሪው 3 ሺህ 275 ሄክታር በክረምት መኽር ዝናብ ቶሎ ደራሽ ማሽላ እና ስንዴ ለመዝራት አሰፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ሶስት የገጠር ወረዳዎች በሚገኙ ማሳዎች ላይ እየለሙ የሚገኙት ሰብሎችም ማሽላ፣ በቆሎ እና ስንዴ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ለመኸር እርሻው ምርትና ምርታማነት ማደግ አስፈላጊው የማዳበሪያ፣ የዘርና ሌሎች የግብርና ግብዓት አቅርቦት ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ያመለከቱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ በምርት ዘመኑ እየለሙ ካሉ ሰብሎች 300 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰበሰብ መታቀዱንም አስረድተዋል።

በየደረጃው ያሉ የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ አስፈላጊውን ሙያዊ እገዛና ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም አርሶ አደሩን ከዝናብ ጠባቂነት ከማላቀቅና ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃር አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።

በቀጣይም የተገኙ አበረታች ውጤቶችን በማስቀጠል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበትና ምርት እና ምርታማነትን ለማሳደግ የላቀ ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

#ኢዜአ

Address

Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aysha ahmed posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category