Jone sufyan

Jone sufyan Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Jone sufyan, Grocers, Harari, Harar.

11/06/2026

በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የምርጫው አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎችን ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ይገመግማል

በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ግምገማ ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ማካሄድ ይጀምራል።

የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የፓርቲው አፈፃፀምና የድህረ ምርጫ ስራዎችን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል።

አቶ ጌቱ በመግለጫቸውም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝባችን ከሌሊት እስከ ሌሊት በመሰለፍ ድምፁን በመስጠት ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነው

በዚህም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ በማካሄድ ኢትዮጵያውያን በፅናት አዲስ ታሪክ ጽፈዋል ብለዋል።

የብልፅግና ፓርቲ አመራርና አባላት የምርጫ ስነ ምግባርን በማክበር ጉልህ ሚና መወጣታቸውን ነው የገለፁት።

ብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መንትያ ግቦችን አስቀምጦ ፣ የምርጫ ቦርድን ህጎች ፣ አዋጅና መመሪያዎች ተከትሎ ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በትብብር እና በፉክክር በመንቀሳቀስ ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ ለምርጫው ሰላማዊነትና ዴሞክራሲያዊነት የሚያስችሉ ስራዎች በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን አብራርተዋል።

ከቅድመ ምርጫ እስከ ምርጫው እለት የታየውን የአመራሮቻችንና የአባላችን የላቀ መናበብ፣ መቀናጀትና ቁርጠኝነት ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የድህረ ምርጫ ሥራዎችን በስኬት በመፈፀምም የተጀመረውን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የብልጽግና ጉዞ ይበልጥ ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

በየደረጃው የሚገኙ የክልሉ አመራሮችን ጨምሮ በሁሉም ወረዳ የሚገኙ የብልፅግና ህብረት አመራሮች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተያዙ መንትያ ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም በቀጣይ ተግባራት ላይ ተግባቦት መፈጠሩን ጠቅሰዋል።

ከነገ ጀምሮም በክልሉ በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ስራዎች እንደሚገመገሙ ጠቁመው በግምገማው ላይም በክልሉ በገጠር እና በከተማ የሚገኙ የፓርቲው አባላት እንደሚሳተፉ ነው የገለፁት።

በመድረኩ ላይም ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም በመገምገም ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞችን እንደሚለዩ አብራርተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ''በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል''።

ስለሆነም በሚካሄደው ግምገማ በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አባላት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ አስተላልፈዋል።

11/06/2026
11/06/2026

ከስድስት ዓመት በፊት የተከሠተውን ለውጥ ተከትሎ በሀገራችን እስከዛሬ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የዴሞክራሲ ምኅዳር ሰፍቷል። ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በሐሳብ የማሸነፍ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

የመደመር መንግሥት ገፅ 282

11/06/2026

በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የምርጫው አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ሥራዎችን ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ይገመግማል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2018 (ኢዜአ)፦ በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ሥራዎች ግምገማ ከነገ ጀምሮ በቀበሌ ደረጃ ማካሄድ ይጀምራል።

የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የፓርቲው አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎችን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል።

አቶ ጌቱ በመግለጫቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ከሌሊት እስከ ሌሊት በመሰለፍ ድምፁን በመስጠት ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነው።

በዚህም ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ በማካሄድ ኢትዮጵያውያን በፅናት አዲስ ታሪክ ጽፈዋል ብለዋል።

ብልፅግና ፓርቲ ግቦችን አስቀምጦ የምርጫ ቦርድን ህጎች፣ አዋጅና መመሪያዎች ተከትሎ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በትብብር እና በፉክክር በመንቀሳቀስ ከቅድመ ምርጫው ጀምሮ ለምርጫው ሰላማዊነትና ዴሞክራሲያዊነት የሚያስችሉ ስራዎች በቁርጠኝነት ሲሰራ መቆየቱን አብራርተዋል።

ከቅድመ ምርጫ እስከ ምርጫው ዕለት የታየውን የአመራሮችና የአባላቱን የላቀ መናበብ፣ መቀናጀትና ቁርጠኝነት ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የድህረ ምርጫ ሥራዎችን በስኬት በመፈፀምም የተጀመረውን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና የብልጽግና ጉዞ ይበልጥ ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችን ጨምሮ በሁሉም ወረዳ የሚገኙ የብልፅግና ህብረት አመራሮች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተያዙ መንትያ ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ስራዎችን በመገምገም በቀጣይ ተግባራት ላይ ተግባቦት መፈጠሩን ጠቅሰዋል።

ከነገ ጀምሮም በክልሉ በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች በጠቅላላ ምርጫው አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ስራዎች እንደሚገመገም ጠቁመው፤ በዚህም በክልሉ በገጠር እና በከተማ የሚገኙ የፓርቲው አባላት እንደሚሳተፉ ነው የገለፁት።

በመድረኩ ላይ ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም እንደሚገመገም አብራርተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል።

በሚካሄደው ግምገማ በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አባላት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑም ኃላፊው ጥሪ አስተላልፈዋል።

11/06/2026

የሴቶች ተሳትፎ በምርጫ ሂደት

ዲሞክራሲ እውነተኛ ትርጉም የሚኖረው፣ የሕዝብ ውክልና የሚረጋገጠውና ዘላቂ ልማት የሚመጣው ሴቶች በፖለቲካና በምርጫ ሂደት ውስጥ ሙሉ፣ እኩልና ንቁ ተሳትፎ ሲኖራቸው ብቻ ነው።

ሴቶች በመራጭነትና በተመራጭነች: በአመራርነት፣ በታዛቢነት እና በጣቢያ አስፈጻሚነት ሚናዎች መሳተፋቸው ሂደቱ ሰላማዊ፣ ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው እሙን ነዉ።

ከለውጡ ወዲህ በኢትዮጵያ የታየው አዲሱ የሴቶች ፖለቲካዊ ጉዞ ምዕራፍ የቁጥር እድገት ብቻ ሳይሆን የጥራትና የውጤታማነት መገለጫ ነው። አንድን አገር ሙሉ ለማድረግ የሕዝቧ እኩሌታ የሆኑትን ሴቶች ማድመጥና ተሳታፊ ማድረግ አማራጭ የለውም።

ሴቶች በፖለቲካው መድረክ በብቃት መሳተፋቸው የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን በተግባር ተረጋግጧል።
የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ማደግ የሴቶች ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የአጠቃላይ አገር ግንባታና የዲሞክራሲ ጉዳይ ስለሆነ የሴቶች ድምፅ ሲደመጥ፣ መብታቸው ሲከበርና በአመራርነት ሲቀመጡ አገር ሰላምና ብልጽግናን ትጎናጸፋለች።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ የመጣው ሀገራዊ ለውጥ በብዙ ዘርፎች አዳዲስ ምዕራፎችን የከፈተ ቢሆንም፣ በተለይ በሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ ረገድ የታየው ተራማጅ እርምጃ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው።

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 50 በመቶ የሚሆነውን የካቢኔ ቦታ ለሴቶች በመስጠት በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ አርአያ መሆን ችላለች።

ለውጡ “ሴቶች ይሳተፉ” ከሚለው የተለመደ መፈክር ባለፈ፣ ሴቶች በውሳኔ ሰጪነት ደረጃ ያላቸውን ተግባራዊ ውጤታማነት ማረጋገጥ መቻሉን በተጨባጭ እያሳየ ይገኛል።

Address

Harari
Harar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jone sufyan posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category