Yahode ያሆዴ Hadiya

Yahode ያሆዴ Hadiya የሀዲያ ታጋይ ልጅ

በኢትዮጵያ ታሪክ ስነዳ ሂደት ሞጋቹ ፕሮፌሰር አርፈዋልላ ጲ ሶ    ጌ ታ ሁ ን    ድ ሌ ቦ (ዶ/ር)ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ በቀድሞው በከንባታና ሐዲያ አውራጃ በኩፋላ ሐበሌ ግንቦት ...
11/10/2025

በኢትዮጵያ ታሪክ ስነዳ ሂደት ሞጋቹ ፕሮፌሰር አርፈዋል

ላ ጲ ሶ ጌ ታ ሁ ን ድ ሌ ቦ (ዶ/ር)

ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ በቀድሞው በከንባታና ሐዲያ አውራጃ በኩፋላ ሐበሌ ግንቦት 12 ቀን 1930 ዓ.ም ተወልደው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቢቾ ሆሣዕና ሚሽን ት/ቤትና በመንግሥት ትምህርት ቤት ሲከታተሉ ቆይተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አዳማ በሚገኘው በአጼ ገላውዴዎስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና ባይብል አካዳሚ ተምረዋል፡፡

ከዚያም ወደ አሜሪካ በማቅናት በኮሙኒቲ ኮሌጅ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው በኀብረተሰብ ታሪክ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል። ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲም በአፍሪካ ታሪክ ጥናት የማስትሬት ዲግሪያቸውን፣ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካና በአውሮፖ ታሪክና በፍልስፍና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ ወስደዋል።

ዶክትሬታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸው ለሁለት ዓመታት በቨርጂኒያ ዩንየን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲያስተመሩ ቆይተው አብዮቱ ሲፈነዳ ‘የታሪክ አካል መሆን አለብኝ’ በማለት ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ያኔ የነበራቸውን ስሜት ሲገልፁ “የኢትዮጵያ አንድነትን እንደ ጣኦት እያመለኩት መጣሁ” ይላሉ፡፡

ወደሀገራቸውም ተመልሰው በዚሁ ስሜትና ሀሳብ ዙሪያም ምርምራቸውንና ማስተማሩን ገፍተውበት አገራቸውን ያገለገሉ ምሁር ናቸው፡፡

በአሜሪካን ሀገር በፍልስፍና እና በታሪክ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ሲማሩ ከአምስት መቶ ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት ከፍተኛ አድናቆት ማትረፍ ችለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በርካታ የአሜሪካን ሀገር ዩንቨርስቲዎች የነፃ የትምህርት ዕድል በአማራጭነት አቅርበውላቸዋል።

ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ ብዙ በተማሩበት ዘርፍ ባደረጉት ምርምር በርካታ የታሪክ መፃህፍትን ያሳተሙ ሲሆን ዐበይት በሆኑ ሀገራዊ የታሪክ ክስተቶችም ላይ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ማለትም በሬዲዮና በቴለቪዥን ላይ በመቅረብ ጠለቅ ያለ ትንተና በመስጠት ይታወቃሉ ፡፡

ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ ካሳተሟቸውም የታሪክ ስራዎች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፡-

1. የኢትዮጵያ የገባር ሥርዓትና ጅምር ካፒታሊዝም፣ 1ኛና 2ኛ የታሪክ መጻሕፍት
2. የኢትዮጵያ ረጅም የሕዝብና የመንግሥት ታሪክ 1ኛ መጽሐፍ፣
3. የኢትዮጵያዊነት ታሪካዊ መሰረቶችና መሳሪያዎች(ታሪክ)
4. የቀይ ባሕርና የዓባይ ሸለቆ ሚና፣ የምፅዋ ሲምፖሲየም-1974
5. የኢትዮጵያ የመከራ ሥርዓትና የኤርትራ ጥያቄ፣ 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ መጽሐፍ
6. አጭር የጌዴኦ ህዝብ ታሪክ ከ1982-1966
7. የምርትና የባህል ዘመቻ በከንባታና ሀዲያ አውራጃ
8. የአዲስ አበባ መዲና እድገትና ሚና በኢትዮጵያ ታሪክ
9. ናሽናል አትላስ እና
10. ሌሎች በርካታ የታሪክ መጻሕፍት አሳትመው ለአንባብያን አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥናት የራሳቸው ፍልስፍና (school of thought) እንዳለቸውም የሚነገርላቸው ፕሮፌሰሩ፣ በዚህም አስተምህሯቸው ምክንያት ብዙ ፈታናዎችን እና ተቃውሞችን ማስተናገዳቸውን በተለያዩ ጊዚያት ከሰጡት ቃለ መጠይቆች ተደምጠዋል፡፡

በባህሪያቸው ግልፅ፣ ታማኝ እና ሰው አክባሪ እንደሆኑ በባልደረቦቻቸው የሚመሰከርላቸው ፕሮፌሰር ላጲሶ “ሰው ሁሉ አንድ ነው፤ ከአንድ ዘር ነው የመጣው፤ ሰውን ከሰው የሚለየው ስራው ነው” ይላሉ፡፡

በአንዳንድ የምርምር ስራዎች ላይ ፈጥነው ወደ ድምዳሜ የሚደርሱ እና ስሜታዊነትንም የሚያንፀባርቁ ሃሳቦችን አካተዋል በሚል ትችት ሲሰነዘርባቸው ይስተዋላል።

“የኢትዮጵያ ታሪክ የሁሉ ካልሆነ የማንም አይሆንም” የሚል መርህ እንዳለቸው የሚናገሩት ፕሮፌሰር ላጲሶ፣ የአንዱን ብሔር ወይም ሐይማኖት ታሪክ ነጥለን ከዚያ አንፃር ብቻ የኢትዮጵያን ታሪክ የምንጽፍ እና የምንተነትን ከሆነ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ታሪክ ማወቅ እንደማይቻል ይናገራሉ፡፡

“የኢትዮጵያ ታሪክ የክርስትናው፣ የእስልምናው እና የሌሎች ሃይማኖቶች እንዲሁም የብዙ ቋንቋዎች እና ህዝቦች መስተጋብር ነው” በሚል ሙግታቸው ይታወቃሉ፡፡

ባለትዳር እና የሦስት ሴት ልጆች አባት የነበሩት የ87 አመቱ የእድሜ ባለፀጋ የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ላጲሶ ድሌቦ ባደረባቸው ህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የእርሳቸው ለኢትዮጵያ ታሪክ ስነዳ ያደረጉት ምርምርና አበርክቶ ግን ለትውልዱ ትልቅ ቅርስ ሆኖ የሚዘልቅ አሻራ ነው።

ምንጭ ፡-
• ታሪካዊ መዝገበ ሰብ (ጌታሁን እንግዳ)
• የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ
• ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ጋር ያደረጓቸው ቃለ ምልልሶች
Yahode ያሆዴ Hadiya

Habayyi 2018 H.D Haddiyyi Yaahode Ugudina Xummine Afisukko !እንኳን ለ 2018 ዓ.ም ለሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ለያሆዴ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! sha...
09/23/2025

Habayyi 2018 H.D Haddiyyi Yaahode Ugudina Xummine Afisukko !
እንኳን ለ 2018 ዓ.ም ለሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ለያሆዴ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! share and like በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ኮከቦች ከፍተኛ የተባለ ሽልማት ተበረከተላቸው  የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2016 ኮከቦች ሽልማትና የማጠቃለያ መርሐ ግብር መስከረም 9/20...
09/20/2024

የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ ኮከቦች ከፍተኛ የተባለ ሽልማት ተበረከተላቸው

የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2016 ኮከቦች ሽልማትና የማጠቃለያ መርሐ ግብር መስከረም 9/2017 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ተካሄዷል።

ጋናዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጫዋች ባሲሩ ኡማረሸ የውድድር ዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ሆኖ የተመረጠ ሲሆን የ210 ሺህ ብር ሽልማት አግኝቷል።

ኤርትራዊው አጥቂ ዓሊ ሱሌማን በ20 ጎሎች የኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ በማጠናቀቁ የ200 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

የዓመቱ ተስፈኛ ወጣት ተጫዋች ሆኖ የተመረጠው የአዳማ ከተማው ቢንያም አይተን የ105 ሺህ ብር ሽልማት ያገኘ ሲሆን የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ፍሬው ጌታሁን ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን የ150 ሺህ ብር ሽልማት አግኝቷል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ አሰልጣኝ በፀሎት ልዑልሰገድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ200 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶለታል።

ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ የዓመቱ ኮከብ ዋና ዳኛ በመሆን የ105 ሺህ ብር ሽልማት አግኝቷል።

በ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16 ተሳታፊ ክለቦች እንደየደረጃቸው የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የሊጉ አሸናፊ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ18 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር በላይ ሽልማት አግኝቷል። ሁለተኛ የወጣው መቻል ከ17 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ ሽልማት ተበርክቶለታል።

ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ ቡና ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ሽልማት ያገኘ ሲሆን አራተኛ የወጣው ባህር ዳር ከተማ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ተሸላሚ ሆኗል።

አምስተኛ ደረጃን ይዞ የጨረሰው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ14 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ አግኝቷል።

በ2016 የውድድር ዓመት የመጨረሻውን 16ተኛ ደረጃ በመያዝ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደው ሀምበሪቾ ከ8 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ሽልማት ተበርክቶለታል።

ክለቦቹ ያገኙት ገንዘብ ከቴሌቪዥን መብት የተገኘ መሆኑን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።

ክለቦቹ ያገኙት የገንዘብ ሽልማት በሊጉ ታሪክ ከፍተኛው መሆኑንም ገልጿል።(ENA)

🔴 መነጣጠል እስከማንችል ተዋሃደናል❗===========================  "ለሁላችንም ዘር አለን። ዘሩ ግን እኛ አይደለንም፤ እኛ ሰዎች ነን  ... መነጣጠል እስከማንችል ተዋሃደናል...
09/18/2024

🔴 መነጣጠል እስከማንችል ተዋሃደናል❗
===========================
"ለሁላችንም ዘር አለን። ዘሩ ግን እኛ አይደለንም፤ እኛ ሰዎች ነን ... መነጣጠል እስከማንችል ተዋሃደናል። የሰው ዲስኩር አንዳችንን ካንዳችን ለማለያየት ስያሜ አበጀልን። ፈጣሪን ለማረም ይመስል እኛም ሆ... ብለን ተከተልን ።

" በሕንድ 2032 ብሔረሰብ በሠላም እየኖረ፤ በቻይና 499 ብሔረሰብ በሠላም እየኖረ፤ እኛ 80 ብሔር መሸከም አቃተን። ተራ በተራ መገዛታችንን ለበላይነት ተጠቀምንበት ። ማንም ከማንም ጋር የዕውቀት እንጂ የሰውነት ጥል ሊኖረው አይችልም። "

እናመሰግናለን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ 🙏

ነፍስዎ በሰላም ትረፍ ...
(ከነቢዩ ሲራክ ገፅ የተገኘ)

[እየጨፈርን ያፈረሰነውን ቤት እያለቀሰን አንገነባውም‼️]"ሁላችንም ዘር አለን፡፡ ዘሩ ግን እኛ አይደለንም! እኛ ሰዎች ነን፡፡ ሰውነት ከመፈጠር እንጂ ከመወለድ አይጀምርምና ፈጣሪ ዘራችንን ...
09/18/2024

[እየጨፈርን ያፈረሰነውን ቤት እያለቀሰን አንገነባውም‼️]
"ሁላችንም ዘር አለን፡፡ ዘሩ ግን እኛ አይደለንም!

እኛ ሰዎች ነን፡፡ ሰውነት ከመፈጠር እንጂ ከመወለድ አይጀምርምና ፈጣሪ ዘራችንን ኢትዮጲያ በምትባል ምድር ላይ ዘራው፡፡ ሲዘራው ኢትዮጲያ ማለት ሰዎች መሆኗን አወቅን፡፡ መነጣጠል እስከማንችል ተዋሃድን፡፡

ትናንት የሆነ የሰው ዲስኩር አንዳችንን ካንዳችን ካልለየሁ እያለ ሥያሜ አበጀልን፡፡ ፈጣሪን ለማረም ይመስል እኛም ሆ ብለን ተቀበልን፡፡ በሕንድ 2032 ብሔረሰብ በሠላም እየኖረ በቻይና 499 ብሔረሰብ በሠላም እየኖረ ምነው እኛ (ሰማኒያዋን) መሸከም አቃተን?ተራ በተራ መግዛታችንን ለበላይነት ተጠቀምንበት? ማንም ከማንም ጋር የሰውነት ጥል ሊኖረው አይችልም የዕውቀት ጥል እንጂ፡፡

ገና ስንወለድ ዘር ምን ይሁን ቋንቋ ምን ይሁን የምናውቀው ነገር አልነበረም፡፡ የዕውቀት ጥል ደግሞ በጠረጴዛ ዙሪያ እንጂ በጦር ሜዳ አይፈታም፡፡ ምክንያቱም ይቅርታ እንጂ በቀል ታሪክን አያርምምና፡፡ ቋንቋ የሚባልን ነገር ከመካከላችን አውጥተን ማሰብ ብንጀምር ዘረኝነት ሃሳብ ላይ እንጂ ደም ላይ እንደሌለ እንረዳለን፡፡ እየጨፈርን የናድነውን ቤት እያለቀስን አንሠራውም፡፡

ሁልጊዜ ጥፋት ካደረስን በኀላ እንዳጠፋን ምንረዳ ከሆነ ዞሮ መልሶ አለማወቅ ይሆንብናል፡፡ በመቻቻል ሳይሆን በፍቅር እንኑር መቻቻል አንድ ቀን ያሰለቸናል፡፡ ታገስኩህ ቻልኩህን ያመጣል፡፡ ፍቅር ግን እስከ ዖሜጋ ይሸከማል፡፡
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
[ Professor Beyene Petros Lodamo]
ለትውልድ ያኖሩት ውርስና ቅርሰ ሁሌም ስታወስ ይኖራል‼️

  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን አርቲስት ሄኖክ ደንኤል መስከረም 05/2017 ዓ/ም ያሆዴን ለማክበር ሀዋሳ ስደማ ባህል አደራሽ ላይ ከላበት በፖሊስ ኃይል ተፍኖ መወሰዱን የያሆዴን ...
09/16/2024



በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን አርቲስት ሄኖክ ደንኤል መስከረም 05/2017 ዓ/ም ያሆዴን ለማክበር ሀዋሳ ስደማ ባህል አደራሽ ላይ ከላበት በፖሊስ ኃይል ተፍኖ መወሰዱን የያሆዴን በዓል ለመክበር የተገኙ እንግዶች ገለፁ።
በሀዲያ ዞን በክልሉ መንግስት ትዕዛዝ ያለ ምንም ጥፋት ወጣቶች እየታሰሩ መሆኑን ከተመኝ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።
የህዝብን ልጅ አርቲስት amile landን በመሰራ የፖለቲካ ጊዜን መራዘም አይቻልም በአስቸኳይ ፍቱት?
ለሀዲያ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ ማቲዎስ አኒዮ
ለማዕከላዊ ኢትዮ/ክልል ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ

ምንጭ: ተስፋሁን ኤርሚያስ

09/04/2024

ስለ ቪዲዮው ጉዳይ አሁን የደረሰኝ መረጃ፣በኢትዮጵያ እና በግብፅ ጉዳይ አይደለም የተደባደቡት❗👇👇
የሶማሌላንድ የፓርላማ አባል የአውደል ግዛት ተመራጭ የሆኑት መሀመድ ሀቢብ በርካታ ደጋፊ ያላቸው ፖለቲከኛ ሲሆኑ በሀገር ክህደት እና የሶማሌላንድ ሪፐብሊክን ከሚቃወሙ ቡድኖች ጋር አብረዋል በሚል September 1ከዱባይ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ሀርጌሳ ኢጋል ኤርፖርት በመንግስት የደህንነት ሀይሎች ከተወሰዱ በሗላ ዛሬ September 3 የሶማሌላንድ የፓርላማ አባላት የመሀመድ ሀቢብ ያለ መከሰስ መብት ለማንሳት ስብሰባ ተጠርቶ የነበረ ቢሆንም ያለመከሰስ መብቱ አይነሳም በሚል ውድቅ አድርገዋል። በአሽቸኳይ የፓርላማ አባሉ እንዲፈቱም
የፓርላማ አባላቱ አሳስበዋል፣ በዚህ ስብሰባ ላይ ያለመከሰስ መብቱ ይነሳ አይነሳ በሚል በተፈጠረ አለመግባባት
ሁለቱ የፓርላማ አባላት እርስበሳቸው ተደባድበዋል በመጀመርያ የተማቱት በርኸት ጃማዕ የተባሉ የፓርላማ አባል መሆናቸውን ገልፀዋል።
=====================
ለፈጣን፣ሚዛናዊ እና አስተማማኝ ወቅታዊ መረጃዎች page like share በማድረግ ይከታተሉ👇👇

ደረሰ..... ደረሰ....በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ድንቅ የሀዲያ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ደረሰ።እንኳን አደረሳቹ እያልኩኝ ያሆዴን በተመለከተ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሳቹ ይህን ገጽ ...
09/03/2024

ደረሰ..... ደረሰ....በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ድንቅ የሀዲያ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ደረሰ።
እንኳን አደረሳቹ እያልኩኝ ያሆዴን በተመለከተ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርሳቹ ይህን ገጽ Like, share, Follow ማድረጋቹን አትርሱ🙏

Yahod photo challenge 🎥
Laxinda modeling squad 🦋💥
SelSeleme Hadiyyaየሀዲያ ቆንጆhYahode ያሆዴ Hadiyaዴያሆዴ መስቀላYahode ያሆዴ Hadiyaያሆዴ ፨Hadiyyaያሆዴ ሆሳዕና

 ! በጥሞና አንብበት!******************************************የሀዲያ ሱልጣኔት በመካከለኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ግዛቶች አንዱ ሲሆን የራሱ የሆነ ጠ...
08/06/2024

!
በጥሞና አንብበት!
******************************************
የሀዲያ ሱልጣኔት በመካከለኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ግዛቶች አንዱ ሲሆን የራሱ የሆነ ጠንካራ ስርወ መንግስት መስርቶ ለብዙ ሺህ ዓመታት ራሱን በራሱ እያስተዳደረ እንደ ሸዋ፣ እንደ ደዋሮ፣ እንደ ዳሞት፣ እንደ ኢፋት፣ እንደ ፈጠጋር ፣ እንደ ዋጅና እንደ አዳል ካሉ ግዛቶች ጋር አብሮ የኖረ ትልቅ ሱልጣኔት ነው።

ይህ ኃያል ሱልጣኔት አሁን ላይ በየቦታው የተበተኑ የተለያዩ ማንነት ያላቸው ህዝቦችን፣ ጠንካራ ወኔ ያለቸው አርብቶ አደሮችን፣ በማይናወጥ መንፈስ የተሸመኑ የሀዲያ ጎሳዎችንና በርካታ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ይዞ ለኑሮ ምቹ ቦታ ፍለጋ ለብዙ ዓመታት በጉዞ እየተመመ የቆየ ትልቅ ሱልጣኔት ነበር።

ሀዲያ ከራሱ አልፎ ከአረብ አገራት፣ ከኢሲያና ከቱርክ ጋር የንግድና የዲፒሎማሲ ግንኙነት የነበረው ብልህና ጥበበኛ ህዝብ ሲሆን ከአርባ ሺህ በላይ ፈረሰኛ የጦር ሠራዊት ያለው የማይደፈር ግዛት የነበረ ህዝብ መሆኑንና በ14ኛው ክፍለ ዘመን "Akuna" የሚባል የራሱን መገበያያ ሳንቲም ቀርጾ ይጠቀም እንደነበር ታዋቂው የፈረንሳይ የታሪክ ተመራማሪ Maurice Gaudefroy ያሳተመውን መረጃ በመጥቀስ Professor Ulrich Braukamper “A History of the Hadiyya in Southern Ethiopia” በሚለው መጽሐፍ ላይ አስፍሯል፡፡

ይህ ሱልጣኔት ምንም እንኳ ኃያል የነበረ ቢሆንም በተደጋጋሚ በደረሰበት የወረራ ጦርነት የሀዲያ ሱልጣኔት መፍረሱንና ከሞት የተረፈው ህዝብ በሌሎች ብሔሮች መዋጡን፣ የተቀረው ህዝብ ደግሞ ዛሬ ወዳለበት ሀዲያ ዞን ውስጥ መስፈሩን ብዙ የታሪክ ተማራማሪዎች ያምናሉ፡፡ በመሆኑም ራሱን በራሱ የማስተደደር ስልጣኑንና መብቱን በሃይል ተነጥቆ ቋንቋውን፣ ሀይማኖቱንና ባህሉን እንዲተው ጭምር ከባድ ጫና እየተደረገበትም ቢሆን በወሻባ የአስተዳዳር ስርዓትና በገራዶች እየተመራ ቆይቷል።

ከእነዚህ የአስተዳደር ስርዓት አንዱ ሲሆን ሶስቱ የሁቤ /Hubanna/ ልጆች ማለትም ራያ ፣ አዘቦ እና አሸንቾ /አሸንጌ የኖሩትን ባህልና ወግ እንደ መስታወት የሚያሳይ ትልቅ የዳኝነት ስርዓት ነው። የሁበና ልጆች ከምዕራብ ጨርጨር እስከ ሽርካ ከሽርካ እስከ ደሎ/ባሌ ፣ ከደሎ/ባሌ እስከ ገደብ /አርሲ ፣ ከገደብ /አርሲ እስከ አባያ ሀይቅ ድረስ ባለው አካባቢ መጠን ሰፊ ግዛት ይዘው ይኖሩ ነበር።

ራያ የራይቱ ሌላ መጠሪያ ሲሆን ጥንታዊ የሀዲያ ጎሳዎች መካከል አንዱ ነው። የዘር ግንዱም በምሥራቅ ባሌ እንዲሁም በሰሜን ኢትዮጵያ ደግሞ ወሎ እና ትግራይ አከባቢ በስፋት ይገኛል።

አዘቦም ከኦሮሞ ጋር ተዋህዶ ማንነቱን በመቀየሩ የተዋጠ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በትግራይ ክልል ራሱን አስጠብቆ ይኖራል።

አሸንቾ በአሁኑ ሀዲያ ዞን ፤ በሲዳማ እና በኦሮሚያ ክልል በስፋት የሰፈረ ሲሆን የሌሞ አባት ጭምር ነው። ሌሞ የአሸንቾ ወይም የአሸንጌ ልጅ ሲሆን የአሸንጌ አባት ሁበና የሁቤ አባት ደግሞ ጡማኖ የጡማኖ አባት ቡቼ ይሆናል። የቡቼ የዘር ሀረግ በሀዲያ ሱልጣኔት ሰፊውን የማህበረሰብ ክፍል ያቀፈ ሲሆን የቀቤና፣ የቡች ሀላባንና የሲዳማ ህዝብን ጨምሮ የዌጦጊራ ፣ የባዴ ጋንሻሮ እና የሌሞ ጎሳዎችን አንድ አድርጎ ይይዛል። አሸንቾ ወይም አሸንጌ በሌላ በኩል የሌሞ ገዥዎች ለባህላዊ አስተዳደር የሚሰጡትን አሸን ገራድ የተባለውን የንግስና ማዕረግ መጠሪያን የሚወክል ነው።

አሸን ገራዶች በሰው ልጆች ማህበራዊ ግንኙነት ከግል ወይም ከቡድን ፍላጎትና ጥቅም እንዲሁም ከሀሳብ ልዩነት የተነሣ የሚከሰቱ ግጭቶችን በመፍታት፣ ግጭትን በማርገብና ጥላቻን በማስወገድ ረገድ ከመደበኛ የፍትህ ተቋማት አገልግሎት ባሻገር በማህበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ እና ባህል የባህላዊ ዳኝነት ዕሴቶችንና ሀገር በቀል ዕውቀቶችን በመጠቀም በጥናትና ምርምር በመታገዝ ለአንድነት ይሰራሉ፤ ጉልህ ሚናም ይጫወታሉ።

ይህ የንግስና ማዕረግ አሰጣጥ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ የመጣ እሴት እንደመሆኑ እስከ ዛሬ ድረስ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተከወነ ቆይቷል። ስለሆነም ዛሬም የሌሞ ህዝብ ዳኛ ብርሃኑ ጡሞሮን የአሸን ገራድ ማዕረግ በመስጠት የተወለዱበትን ህዝብ እንዲያገለግሉ ሌሎች የሀዲያ ሽማግሌዎች ፣ ገራዶች፣ አበጋዞች ፣ የመንግሥት አካላትና የተለያዩ ምሁራን በተገኙበት በአንድነት ሄቦ ተብሏል።

Mahaar Iyyona ይባላል !

07/22/2024

ሰላም የሀዲያ ልጆች በያላቹበት ሰላማቹ ብዝት ይበልልኝ።

Address

, , Churchill Road
New York, NY
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yahode ያሆዴ Hadiya posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yahode ያሆዴ Hadiya:

Share