02/11/2025
ህብረ ብሄራዊነት፣ አሳታፊነት ፣ ብዝሃነት እና አቃፊነት የብልፅግና ፓርቲ መገለጫ ነው ።
አቶ ትግሉ ገብሬ
የአዲስ ከተማ ወረዳ 4 ብልፅግና ፓርት ቅ/ጽ/ቤት
የብልፅግና ፓርቲ ዋና አላማ ህብረ ብሄራዊነቱን የጠበቀ እና የጋራ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያለው ማህበረሰብ መገንባት ነው።
ስለ ህብረ ብሄራዊነት ስናወራ ሁሉንም ብሔረሰቦችን ፣ ኃይማኖቶችን ወይም ማንነቶችን ያካተተ ነገር ግን የትኛውንም ብሔር የማያገለል ማለታችን ነው።
የብልፅግና ፓርቲ ህብረ ብሄራዊነት በአሳታፊነት ፣ ብዙሃነት እና አቃፊነት መገለጽ አለበት ብሎ ያምናል።
ህብረ ብሄራዊ አንድነት ብዘኃነትን እንደ ልዩ ሥጦታ ይመለከተዋል። ህብረ ብሄራዊ አንድነት የእርስ በርስ መተሳሰራችን መገለጫ እና የጠንካራ አንድነታችን ምልክት ነው። ህብረ ብሄራዊ አንድነት የሚያሳየው እጣ ፈንታችን በቅርበት የተሳሰረ መሆኑን ተገንዝበን በጋራ መቆም ፣ መረባረብ እና ለጋራ አላማ መቆም እና መደጋገፍ እንዳለብን ነው።
ህብረ ብሄራዊ አንድነት የጋራ የማንነታችን መገለጫ ፣ የአንድነታችን እና የጠንካራ ትስስራችን ምልክት ነው። የህብረ ብሄራዊ አንድነት የሚያሳየው እጣ ፈንታችን በቅርበት የተሳሰረ መሆኑን ተገንዝበን በጋራ መቆም ፣ መረባረብ እና ለጋራ አላማ መቆም እና መደጋገፍ እንዳለብን ነው።
ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ብዙ ሆነን አንድ አንድ ሆነን ብዙ በመሆን ለጋራ ዓላማና ተልዕኮ የተሰባሰብንበት አንድነት ነው።
በብዝሃነታችን ውስጥ እየበራን በአንድነታችን ጠንክረን መገስገስ የውበታችንና የጥንካሬያችን ምንጭ ነው።
ፍትህ ከተረጋገጠ ሰብአዊ ክብር ከሰፈነ ብልፅግና ከመጣ እንደ ሀገር ቀጣይነታችን ይለመልማል። ነገር ግን የጋራ ህብረ ብሄራዊነት እነዚህ ምሰሶዎች ከተሳኩ ብቻ ሳይሆን ለዓላማው መሳካት የበኩላችንን ሚና እንድንጫወት ስለሚያስችሉን በጋራ ወደ ብልፅግና እንሄዳለን በሚለው መመሪያ መሰረት ፓርቲያችን ብልጽግና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።