ተስፋ አለኝ በሀገሬ

ተስፋ አለኝ በሀገሬ I love Ethiopia & Ethiopian

ኢትየጵያ የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታዋን (Ethiopia National Energy Compact) በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባኤ ላይ አቀረበች - የካቲት 26/2018...
06/03/2026

ኢትየጵያ የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታዋን (Ethiopia National Energy Compact) በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባኤ ላይ አቀረበች - የካቲት 26/2018 ዓ/ም

ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ በዓለም ባንክ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ በጋራ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው እ.ኤ.አ እስከ 2030 ድረስ 300 ሚሊዮን አፍሪካውያንን የኤሌክትሪፊኬሽን አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያልመው ጉባኤ (Mission 300) ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች፡፡

በጉባኤው የዘርፉ እና የፋይናንስ ሚኒስትሮች፣ ለጋሽ እና አበዳሪ ድርጅቶች፣ የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድረሻዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር የተከበሩ ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ በጉባኤው የከሰዓት በኋላ መድረክ ላይ የኢትዮጵያን የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታ (Ethiopian National Energy Compact) አቅርበዋል፡፡

የፍኖተ ካርታው የኤሌክትሪክ እና የንጹህ ማብሰያ ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን፣ ብርቱ የኃይል መሰረተ ልማትን ማጠናከር፣ ቀጣናዊ የኃይል ሽያጭ የገበያ ድርሻን ማሳደግ፣ የዘርፉን ተቋማት አቅም ማሳደግ እንዲሁም የግሉን ዘርፍ ማሳተፍ የሚሉ አምስት ዋና ዋና አምዶች እንዳሉት አብራርተዋል።

መንግሥት ለዜጎች ተደራሽ የሚሆን የኤሌክትሪፊኬሽን አገልገሎትን ዕውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ በምስራቅ አፍሪካ በኃይል ማመንጨት እና ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድ ያላትን ጉልህና ቀዳሚ ሚና ለማሳደግ እየሰራች እንደምትገኝ አስረድተዋል፡፡

ፍኖተ ካርታው እ.ኤ.አ እስከ 2030 ድረስ አሁን ያለውን የኤሌክትሪፊኬሽን ሽፋን ተጨማሪ 50 ሚሊዮን ህዝቦችን ተጠቃሚ በማድረግ ወደ 75 በመቶ ከፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነ ገልጸዋል።

የንጹህ ማብሰያ ቴክኖሎጂ አቅርቦትን ደግሞ ወደ 58 በመቶ ማሳደግ የፍኖተ ካርታው ትኩረት እንደሆነም አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ የምታመርተው ኤሌክትሪክሲቲ 100 በመቶ ከታዳሽ የኃይል ምንጭ እንደሆነ ለመድረኩ የገለጹት ክቡር ሚኒስትሩ፤ በቀጣይ እ.ኤ.አ እስከ 2030 አጠቃላይ አገሪቱ የማምረት አቅሟን ወደ 14 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ እየሰራች እንደምትገኝ አብራርተዋል፡፡

ከመድረኩ ተሳታፊዎች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡት ክቡር ሚኒስትሩ፤ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች ኢትዮጵያ ውስጥ በዘርፉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበው፤ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

ስንዴ፡ ከምግብነት በላይ የድል አርማ! 🌾ራሱን የሚመግብ ህዝብ ክብሩ የላቀ ነው! ዛሬ በገዛ መሬታችን የምናመርተው እያንዳንዱ የስንዴ ዘር የነፃነታችን ማረጋገጫ ነው። ብልፅግና በምኞት አይመ...
17/02/2026

ስንዴ፡ ከምግብነት በላይ የድል አርማ! 🌾
ራሱን የሚመግብ ህዝብ ክብሩ የላቀ ነው! ዛሬ በገዛ መሬታችን የምናመርተው እያንዳንዱ የስንዴ ዘር የነፃነታችን ማረጋገጫ ነው። ብልፅግና በምኞት አይመጣም፤ ብልፅግና የከባድ ስራ ውጤት ነው። ክብራችንን በተግባር፣ ሉዓላዊነታችንን በምርታችን እናረጋግጣለን! 🇪🇹✨
#ልማት #ኢትዮጵያ
Oomisha Qamadii: Mallattoo Ijaarsa Biyyaa! 🌾
Qamadiin nyaata qofa osoo hin taane, mallattoo ofiin of danda’uu keenyaati. Harka namaa eeggachuu dhiisnee, oomisha keenyaan of sooruun injifannoo guddaadha. Badhaadhinni kan mirkanaa’u abjuu qofaan osoo hin taane, hojii jabaa fi kutannoodhaani! 💪🇪🇹

Hojii 7/24 Daandii Jijjiiramaa Irra
05/01/2026

Hojii 7/24 Daandii Jijjiiramaa Irra

04/09/2025
ግብፅ vs ኢትዮጵያ\nየግብፅ እና የኢትዮጵያ ጨዋታ አርብ ምሽት በኢትዮጵያ አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ እመኛለሁ!
04/09/2025

ግብፅ vs ኢትዮጵያ\n

የግብፅ እና የኢትዮጵያ ጨዋታ አርብ ምሽት በኢትዮጵያ አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ እመኛለሁ!

28/08/2025

በውሃና ኢነርጂ ሚነስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር/ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የቅድመ ሁለተኛ የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ የኢነርጂ አውደ ርዕይን በይፋ የከፈቱበት አና ከአለም አቀፍ ሶላር አሊያንስ (ISA) ጋር የፀሃይ ኃይል ፕሮጀክቶች በተፈራረሙበት ወቅት ካደረጉት ውይይት የተቀነጨበ።

እንዴት ናቹ EP?! የአዲስ አበባ ከተማ የአረንጓዴ ልማት ከ2.8% ወደ 20% ሽፋን እድገት አሳይቷል በተጨማሪ ከ76 የከተማ ውስጥ የወንዝ ዳርቻዎች ፅዳትና ለእይታ ሳቢ የማድረግ ስራ ተጠና...
10/06/2025

እንዴት ናቹ EP?! የአዲስ አበባ ከተማ የአረንጓዴ ልማት ከ2.8% ወደ 20% ሽፋን እድገት አሳይቷል በተጨማሪ ከ76 የከተማ ውስጥ የወንዝ ዳርቻዎች ፅዳትና ለእይታ ሳቢ የማድረግ ስራ ተጠናቋል; እንዲሁም ከ454 በላይ ዘመናዊ እና ፅዱ የመፀዳጃ ቦታዎችን ሰርቶ በማጠናቀቅ ለከተማው ነዋሪ ክፍት ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የተከበሩ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
በመሆኑም ስራው ተሰርቷ እኛ የEP አባላት የተሰራውን ስራ የመጠበቅ እና የማሳደግ ኀላፊነት አለብን;,...guys sustainability matters.
እንዲሁም የኢፌድሪ ጠ/ሚ ክቡር ዶ.ር አብይ አህመድ በ4 ተከታታይ ፕሮግራም በሰጡት ወቅቱን የጠበቀ ሃገራዊ ገለፆ ግልፅ እንዳረጉት "ሰርቶ ለመለወጥ ዝግጁ ለሆነ ኢትዮጵያዊ አሁን አመቺ ጊዜ ነው" ብለዋል,
መንግስት አገልጋይ ነው እንዲሁም ማንም ለማገልገል ዝግጁ የሆነ ኢትዮጵያዊ የእናቴ መቀነት ጠለፈኝ ሳይል ለመጪው ትውልድ የበለፀገች ሃገር ለማስረከብ መንግስትን በሚችለው እንዲያግዝ ደጋግመው ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም መንግስት ከግል ጥቅም ይልቅ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ እና ለዚህም እየተሰሩ ያሉ የልማት አቅጣጫዎች ማሳያ እንደሆኑ በፈረንሳይ ሃገር የተገነባውን የካቶሊክ ሮተርዳም ቤ/ክ የግንባታ ሂደት ከ200 ዓመት በላይ እንደወሰደ እና ይህ የቤ/ክ ግንባታ ፕሮጀክት ምን ያክል ለትውልድ ታልሞ የታነፀ እንደሆነ በማንሳት;
መንግስት መሬት ላይ ያሉትንም ሆነ በወረቀት የሰፈሩ የልማት ስራዎችን አሻግሮ ለትውልድ ያቀዳቸው መሆኑን ገልፀዋል!

በመሆኑም ውድ የEP አባላትና የአዲስ አበባ ወጣቶች,...ትናንት የለም, ዛሬ እጃችን ላይ ነው!, ነገ ደግሞ የማን እንደሆነ አይታወቅም።
ስለዚህ ዛሬ ለትውልድ የሚሆን አሰደማሚ ስራን ሰርተን ለማለፍ በምንችለው ሁሉ መንግስትን በማገዝ የበለጠ መንቀሳቀስ ይኖርብናል።

Ethiopian prevails!!

በበጀት ዓመቱ ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።አዲስ አበባ: የካቲት 13/2017 ዓ.ም የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር...
21/02/2025

በበጀት ዓመቱ ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

አዲስ አበባ: የካቲት 13/2017 ዓ.ም የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግሟል።

በግማሽ ዓመቱ የድንበር እና ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ተጠቃሚነት፣ የናይል ተፋሰስ ሀገራት የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት እና አተገባበር፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ጥራት እና ፍትሃዊ ተደራሽነት ላይ በርካታ ተግባራት መከናወኑ ተገልጿል።

በዕለቱ የውኃ ሃብት አሥተዳደር እና አጠቃቀም፣ የአገልግሎት አሰጣጥ እና ተቋማዊ የማሥፈጸም አቅምን ማጎልበት እንደሚገባ የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ.ር) ተናግረዋል።

በከተማ እና በገጠር ያሉ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ መኾኑን በመድረኩ የተሳተፉ የክልል ውኃ እና ኢነርጂ ቢሮ የሥራ ኀላፊዎች ገልጸዋል።

በተለይም በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎችን በመለየት በመንግሥት እና መንግሥታዊ ባልኾኑ ረጅ ድርጅቶች ትልልቅ የውኃ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ሥለመኾኑም ተሳታፊዎቹ አንስተዋል።

እንደ ሀገር "በበጀት ዓመቱ 460 ሺህ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ለማድረግ የታቀደ ሲኾን እስካሁን ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን" የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገልጿል።

በድርቅ የሚጠቁ የኦሮሚያ፣ የአማራ እና የአፋር ክልሎች አምስት ትልልቅ የውኃ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ሲኾን ከነዚህም ሁለቱ ተገንብተው አገልግሎት እየሠጡ ነው ተብሏል።
Ministry of Water and Energy - Ethiopia
Habtamu Itefa
Lensa Inkosa

Address

Addise
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተስፋ አለኝ በሀገሬ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category