በማዕ/ኢት/ክ/መንግስት የሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም

በማዕ/ኢት/ክ/መንግስት የሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ይህ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም የፌስቡክ ገጽ ነው ።

‎የጓደኛውን ሞተር ቁልፍ በመስቀረጽ ሞተሩን ሰርቆ ወደ ኦሮሚያ ክልል የሸሸገው ተጠርጣሪ ከና ግብረአበሮቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ ።‎‎በቀን 03/2018 ዓ.ም በሀለባ ቁሊቶ ከተማ ሜጦማ ቀ...
10/06/2026

‎የጓደኛውን ሞተር ቁልፍ በመስቀረጽ ሞተሩን ሰርቆ ወደ ኦሮሚያ ክልል የሸሸገው ተጠርጣሪ ከና ግብረአበሮቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ ።

‎በቀን 03/2018 ዓ.ም በሀለባ ቁሊቶ ከተማ ሜጦማ ቀበሌ ልዩ ስሙ መቀላ ተራ አከባቢ አቶ ነብዩ ጀማል የተባለው ግለሰብ የጓደኛውን የነጃ እማም ሀሱኔ አፓቺ ሞተር ሰይክል ቁሊፉን በማስቀረጽ ሞተሩን ወስዶ አቶ ህርጰ አማን ኦሮሚያ ክልል በሳ ቀበሌ ነዋሪ 2ተኛ ቦንሲ ወንባሪ በተመሳሳይ የባሳ ነዋሪ 3ተኛ ቦሪ ቦንሲ ስራሮ ወረዳ 4ተኛ ኑራ መሸሻ የባሳ ነዋሪ ሲሆኑ ሞተሩን ወደ ኦሮሚያ ክልል በሳ ቀበሌ ወስደው ከሸሸጉበት የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ፖሊስ ጥብቅ ክትትልና ጠንካራ ኦፕሬሽን ስራ በመስራት ተጠርጣሪውን ከና ግብረአበሮቹጋ በቁጥጥር ስር መዋል ችሏል።

‎ ወንጀልን በጋራ እንከላከል !!
‎የሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት ።
‎ዘጋባው የሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅ/ቤት ህዝብ ግንኘነት ነው!!!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል መንግስት ሪዕሰ መስተዳድር ቢሮና የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ የተወጣጠ ድጋፍና ክትትል ቡድን የሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋምን በቼክሊስት ድጋፋዊ ክትትል አደረገ።*ሰኔ ...
10/06/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል መንግስት ሪዕሰ መስተዳድር ቢሮና የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ የተወጣጠ ድጋፍና ክትትል ቡድን የሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋምን በቼክሊስት ድጋፋዊ ክትትል አደረገ።
*
ሰኔ 03/2018 ዓ.ም ቁሊቶ፤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል መንግስት ሪዕሰ መስተዳድር ቢሮ እና ሠላምና ፀጥታ ቢሮ የተወጣጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላት የሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋምን በዛሬው ዕለት በቼክሊስት ድጋፋዊ ክትትል አድርገዋል።

የሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ረ/ኢንስፔክተር ሁሴን ጉንታ ለድጋፋዊ ክትትል የመጡ ቡድን አባላትን አመስግነዉ በቼክሊስት ለቀረበላቸው መጠይቅ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የድጋፍና ክትትል ቡድኑ ሰብሳቢና የክልሉ የሪዕሰ መስተዳድር ቢሮ የህግና የመልካም አስ/ር ጽ/ቤት የፎርም፣ የፀጥታና ህግ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ኦሰቦ ካልቲሶ እንደገለፁት ተቋሙ የህግ ታራሚዎች ታርመዉና ታንፀዉ እንዲወጡና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ በትምህርትና ሙያ ስልጠና የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዉ፤ የማረሚያ ቤቱ መንግስትን ሳይጠብቅ የግቢዉን እርሻ ቦታ በፍራፍሬ፣ በአትክልትና ሰብሎች በመሸፈን እንዲሁም ለተለያየ አገልግሎት የሚዉሉ ግንባታዎችን በማከናወን የዉስጥ ገቢን ለማሳደግ እየሰራ ያለውን ተግባር አድንቀዋል።

የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ቤት በእርምት ላይ የሚገኙ የህግ ታራሚዎችን የጎበኘ ሲሆን የታራሚዎች የመኝታ፣ የምግብ፣ የዉሃና የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን እንዲሁም የታራሚዎች የንጽሕና አጠባበቅ፣ የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ የሃይማኖትና ዕምነት ነፃነት ጥበቃ፣ የስፖርታዊ እንቅስቃሴና መዝናኛ ቦታዎች፣ የትምህርትና ሙያ ስልጠና ማህበራት እንቅስቃሴና ልዩ ትኩረት የሚሹ የህግ ታራሚዎችን እንክብካቤ አያያዝ ሂደትን ጉብኝትና ምልከታ አድርገዋል።

ሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ በድሪያ ጎዶ ሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ተስረው ለሚገኙ ለሴት ህግ ታራሚዎች ሥራ ዕድል እንድያገኙ የሻይ ቡና ሙሉ ዕቃ ድገፍ አደረገች።።።።...
07/06/2026

ሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ በድሪያ ጎዶ ሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ተስረው ለሚገኙ ለሴት ህግ ታራሚዎች ሥራ ዕድል እንድያገኙ የሻይ ቡና ሙሉ ዕቃ ድገፍ አደረገች።።።።።።።።
በማቃጣል ምግቤን ከጎሮዬ በሚል ለሴት ታረሚዎች ጎመን ተክለው እንድጠቀሙ ተቋሙ ቦታ ተሰተቸው ጎመን ተከላ አከሄዱ።

ቀን 29/9/2018 ዓ.ም ዋንዛ በር ቃላ ህይወት ቤተክርስቲያን ለሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ተስረው ለሚገኙ ህግ ታረሚዎች የምሳ ግብዥ አደረጉ ።።።።።።።።በምሳ ግብዥ ፕሮግራም የቤተክ...
07/06/2026

ቀን 29/9/2018 ዓ.ም
ዋንዛ በር ቃላ ህይወት ቤተክርስቲያን ለሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ተስረው ለሚገኙ ህግ ታረሚዎች የምሳ ግብዥ አደረጉ ።።።።።።።።
በምሳ ግብዥ ፕሮግራም የቤተክርስቲያኑ መጋብ አቶ ሠለሞን ዮሴፍ ተገኝተው የህግ ታራሚዎችን ኢ/አቤር ይፍታችሁ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፏል ።
በማቃጠል የተቋሙ መሠረታዊ ፍላጎት አስተባባሪ እና የተቋሙ ኃላፍ ተወካይ ዋ/ሣጅን ሙስባ ከድር ይህንን የምሳ ግብዥ ብዙ ወጪ አወጥታችሁ በጉልበት ለፍታችሁ ለነዚህ ታራሚዎች አስባችሁ የማጠችሁ የቤተክርስቲያኑ አስተባባሪዎች ፣እናቶችና ወጣቶች እንዲሁም የተቋማችን ወ/ላዊ አበበ ብሸው በተቋሙ ስምና በረሴ ለቅ ያለ ምስጋና አቀርበዋለሁ

የቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ከለዉጡ ቡኃላ የመጡ ለውጦች ተጠናክረው ቀጥለዋል ።በመረምና ማነፅ ረገድከሀላባ ዞን ፖሌ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር የህግ ታራሚዎች የሙያ ስልጣና ማለትምየልብስ ስፌት...
05/06/2026

የቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ከለዉጡ ቡኃላ የመጡ ለውጦች ተጠናክረው ቀጥለዋል ።
በመረምና ማነፅ ረገድ
ከሀላባ ዞን ፖሌ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር
የህግ ታራሚዎች የሙያ ስልጣና ማለትም
የልብስ ስፌት ፣የጣውለ ሥራ በማህበር፣
የልማት ሥራ የአበሸ ጎመን ተከለ ፣የጥቅል ጎመን ተከለ፣የካሮት ፣ ዛመናዊ የዓሣ እርባታ ግንባታ ሥራ የቡሎኬት ሥራ ፣የዶሮ እርባታ ፣በተለይ አንድም መሬት ፆም ማደሪ የለበትም በሚል ተቋሙ በትኩረት እየሣረ ይገኛል።
ማረሚያ ተቋም ታረሚዎች
ተስረው የሚኖሩባት ሰይሆን
ሙያ ቀስሞ የሚውጡበት
የልማት አሪአያ ሆኖ የሚውጡባት
አምራች ዜጋ ሆኖ የሚውጡባት
ተቋም ነው ።
የታረመ ና የተነፀ ዜጋ እንፈጥራለን !!!

የሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም የፖሊስ አባላት  7ተኛ ሀገራዊ  ምርጫ  ጉራጌ ዞን ሄደው ምርጫውን በሰለም አጠነቅቀው  ወደ  ሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ገብቷል።የተቋሙ ኃላፍ ኢ/ር ሁ...
04/06/2026

የሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም የፖሊስ አባላት 7ተኛ ሀገራዊ ምርጫ ጉራጌ ዞን ሄደው ምርጫውን በሰለም አጠነቅቀው ወደ ሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ገብቷል።
የተቋሙ ኃላፍ ኢ/ር ሁሴን ጉንታ እንኳን በሠለም መጣችሁ ኮርታንባቸዋል ጀግኖች በማለት በጣም ጥሩ አቀባበል አድርጓል

በሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋም በበልግ እርሻ ወቅት የተዘረ የደረሰ የበርበሬ ችግኝ እየተተከለ ይገኛል።
04/06/2026

በሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋም በበልግ እርሻ ወቅት የተዘረ የደረሰ የበርበሬ ችግኝ እየተተከለ ይገኛል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ ምንም የጸጥታ ስጋት በሰላም መጠናቀቁን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ሆሳዕና፣ግንቦት 25/2018) የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን  የሰባተኛው ጠቅላላ...
02/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ ምንም የጸጥታ ስጋት በሰላም መጠናቀቁን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ

ሆሳዕና፣ግንቦት 25/2018) የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት መጠናቀቁን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሳ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ ምንም የጸጥታ ስጋት በሰላም ተጠናቋል ብለዋል።

በክልሉ እስከ ታችኛው መዋቅር የጸጥታ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ ወደ ተግባር መገባቱን ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

ማህበረሰቡን በጸጥታ ስራ ማሳተፍ አብይ አጀንዳ እንደነበር ያስታወሱት ኮሚሽነሩ ይህም አስቀድሞ ወንጀልን በመከላከል ረገድ የላቀ አበርክቶ ነበረው ሲሉም ጠቁመዋል።

ወጣቶችን፣ሴቶችን፣የሀይማኖት አባቶችን እና የሀገር ሽማግሌዎችን ያሳተፈ ውይይት ማካሔድ በመቻሉ የወንጀል መከላከል ስራው ስኬታማ መሆኑን ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።

የክልሉን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ከተከናወኑ ተግባራት ውስጥ የገለልተኛ አማካሪ ምክር ቤት እና የጸጠሰታ ምክር ቤት ማጠናከር ተጠቃሽ መሆኑን ኮሚሽነር ሽመልስ በመግለጫቸው ጠቅሰዋል።

ከክልሉ ፍትህ ቢሮ ጋር በመቀናጀት በህግ የሚፈለጉ ተጠርጣሪዎችን በማቅረብ እና ምርመራ በማካሔድ ህግ የማስከበር ስራ ማከናወን ስለመቻሉም ተናግረዋል።

የክልሉ አጠቃላይ የጸጥታ ሁኔታ በክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ በየጊዜው እየተገመገመ መሆኑን የተናገሩት ኮሚሽነሩ በዚህም አስተማማኝ እና ዘላቂ ሰላም በመገንባት ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።

ከምርጫ በፊት የጸጥታ ሀይሉን የማጠናከር ስራ ልዩ ትኩረት እንደተሰጠው የጠቆሙት ኮሚሽነሩ በዘርፉ ተጨማሪ የሰው ሀይል በማሰልጠን ወደ ስራ መግባቱን ጠቅሰዋል።

የጸጥታ ሀይሉን በምርጫ ስነ ምግባር ላይ አስቀድሞ ግንዛቤ እንዲጨብጥ በማድረግ የጋራ ተግባቦት በመፍጠር ወደ ተግባር መገባቱን ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በክልሉ 35 የምርጫ ክልሎች እና 2ሺ 998 የምርጫ ጣቢያዎች እንደነበሩ ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው አውስተዋል።

በክልሉ በሁሉም የየምርጫ ጣቢያዎች የጸጥታ ሀይል በመመደብ ወደ ተግባር መግባት መቻሉን የገለጹት ኮሚሽነር ሽመልስ ተጨማሪ እገዛ በሚያስፈልጋቸው አካባቢዎች የክልሉ አድማ ብተና ፖሊስ፣የፌደራል ፖሊስ እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት ባላት ስምሪት ወስደው ድጋፍ ሲያደርጉ እንደነበርም አብራርተዋል።

በምርጫ በሂደቱ ያጋጠሙ ቀላል ጉዳዮች ከምርጫ አስተባባሪዎች ጋር በመነጋገር መፍታት መቻሉን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል ።

በክልሉ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ያጋጠመ የጸጥታ ችግር አለመኖሩን የገለጹት ኮሚሽነሩ በዚህም ህብረተሰቡ በነጻነት ድምጽ በመስጠት ወደ መደበኛ ስራው መሰማራቱን በመግለጫቸው አብራርተዋል።

አብዛኛው የምርጫ ቁሳቁሶችን ወደ ምርጫ ክልል የማጓጓዝ ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።

የዘንድሮው ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን የክልሉ ህዝብ፣ፖሊስ፣የድማ ብተና ኃይል፣ቪአይፒና ተቋማት ጥበቃ ሻለቃ፣ማረሚያ ቤቶች፣የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፌደራል ፖሊስ፣የሚሊሻ አባላት፣የክልል፣የዞን ፣የልዩ ወረዳ፣የወረዳ፣የከተማ አስተዳደር እስከ ቀበሌ ያለው አመራር ለጸጥታ ስራው የላቀ ድጋፍ በማድረጋቸው ኮሚሽነሩ ምስጋና አቅርበዋል።

ቁሊቶ ከተማ አማኑኤል ቤተክርስቲያን በዛሬው ቀን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ተስረው ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች የልብስ ሳሙና ና አልባሳት እንድሁም ለሴት ህግ ታረሚዎች የንፅህና መጠበቂያ ድጋፍ አደረገ...
31/05/2026

ቁሊቶ ከተማ አማኑኤል ቤተክርስቲያን በዛሬው ቀን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ተስረው ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች የልብስ ሳሙና ና አልባሳት እንድሁም ለሴት ህግ ታረሚዎች የንፅህና መጠበቂያ ድጋፍ አደረገ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ግንቦት 23/9/2018 ዓ.ም
ቤተክርስቲያኑ ለዚህ ጠያቂ ለሌላቸው ታረሚዎች ይህንን ልብስ ና ሳሙና ብዙ ለፍታችሁ ወጭ አርጋች ለመጣችሁ የአማኑኤል ቤተክርስቲያን አስተባባሪዎች፣እናም የተቋማችን ወ/ላዊ አበበ ብሸው ጭምር የተቋሙ ኃላፍ ተወካይ ዋ/ሣጅን ሙስባ ከድር በፕሮግራሙ ለይ ተገኝተው ላቅ ያላ ምስጋና አቅርበዋል ።

ወደ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ ተያዘበዲላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለታራሚ ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ መያዙን ተቋሙ አስታውቋል።ግንቦት 22 ቀን 20...
30/05/2026

ወደ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ ተያዘ

በዲላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለታራሚ ሊገባ የነበረ ሞባይል ስልክ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ መያዙን ተቋሙ አስታውቋል።

ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም

ወ/ሪት ንግስት ይጨነቁ የህግ ታራሚ ዘመድ ጠያቂ በመምሰል ወደ ተቋም እንዳይገባ የተከለከለ ሞባይል ስልክ በእግሯ ላይ በማሰር ለማስገባት ስትሞክር በዕለቱ ተረኛ ሴት ፈታሽ ፖሊስ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ ተይዛለች።

የተቋሙ አዛዥ ኢንስፔክተር ትዕግስት ሮቤ እንደገለፁት የህግ ታራሚ ዘመድ ጠያቂዎች ለማረም ማነጽ ስራ አጋዥ መሆን ስገባ ይህን ያህል አስነዋሪ ተግባር መፈጸም ተገቢ አለመሆኑን አሳስበው ወ/ሪት ንግስት ይጨነቁ በዲላ ከተማ ፖሊስ ምርመራ እንዲጣራ መላኳን አስታውቀዋል።

በስተመጨረሻ የተከበረው የዲላ ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች የማረም ማነጽ ተግባር የሁሉ ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን በመገንዘብ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ምንጩ ከድላ ማረሚያ ተቋም ህዝብ ግንኘነት ነው !!

Address

Alaba Kulito
Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕ/ኢት/ክ/መንግስት የሀላባ ዞን ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share