Abrish Negn Kewubitu Dangila

Abrish Negn
Kewubitu Dangila Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Abrish Negn
Kewubitu Dangila, Grocers, abrahamgetahun09@gmail. com, Bahir Dar.

14/10/2025

#መምህር
*******
አንተ የቀለም ሰው ጥበብ አስተማሪ
የአለምን ሚስጥር በሙያህ መርማሪ
የሰው ግርድና ምርት ሁልጊዜ አበጣሪ
ስራህ የሚያኮራህ ትውልድ አሳማሪ
ተጨንቀህ ተጠበህ አዲስ ሰው ፈጣሪ
አንተ ነህ መምህር ስልጣኔ አብሳሪ።
ጨቅላ ህፃናትን ኮትኩቶ አሳዳጊ
መሃይምነትን ዘወትር ተዋጊ
በየትኛውም ቦታ ሙያህ ተፈላጊ።
እውቀትን ለመዝራት አቋርጠህ ተራራ
በሀሳብ ማዕበል ስትበር እንደ አሞራ
ብጤህን ለማፍራት ፍቀህ ነጭ አቧራ
መምህር አይታክትህ ሙያህን ስትዘራ
የስልጣኔ ምንጭ ያንተ ቅዱስ ስራ
ለአዳዲስ ግኝቶች የእድገት አሻራ

አስተካክለህ ስለህ የሰውን አእምሮ
ፍጡር ሰው እንዲሆን አውቆ ተመራምሮ
ጥበብ ፍልስፍናን ህሊናን ቀምሮ
ሁሉን ያዳርሳል በጊዜ ቀጠሮ።

ክብርና ምስጋና ለመምህራኖች🙏

Enkon yewerhawi yebeleweld beal beselam aderesachh aderesan Sile beleweld debo yezu"እንቁላሉ ስንት ስንት ነው?" ስትል ጠየቀቻቸው"አንዱ እን...
04/09/2025

Enkon yewerhawi yebeleweld beal beselam aderesachh aderesan
Sile beleweld debo yezu

"እንቁላሉ ስንት ስንት ነው?" ስትል ጠየቀቻቸው
"አንዱ እንቁላል 4 ብር ነው " ልጄ በማለት መለሱ፣
#እማማ…"አምስቱን እንቁላል በ10 ብር ልውሰደው?…" ስትል ደግማ ጠየቀቻቸው …

"አይጎዳኝም ብለሽ ነው ልጄ?"…በማለት ደከም ባለ ድምፅ መለሱላት…

"ከፈለጉ ይሽጡ፣ ካልፈለጉ ግን በቃ መሄዴ ነው…" አለች፣ ጠንከር ባለ ድምፅ…

#እማማ ትንሽ አሰቡና ቀና ብለው አይተዋት…
"እስካሁን ምንም አልሸጥኩም፣ ➢ባያዋጣኝም እንደ መጀመሪያ ገድ ልቁጠረውና ልሽጥልሽ፣ የፈለግሺውን ያህል እንቁላል በፈለግሺው ዋጋ ውሰጂ…" ሲሉ በደከመ ድምፅ ተናገሩ…

ዘንቢሏን አውጥታ 5 እንቁላል መርጣ አስገባች፣ ከበርካታ 100 ብሮች መካከል ነጠላ 10 ብር አውጥታ ወርውራላቸው እየተጣደፈች የሚያምረው ዘመናዊ መኪናዋ ውስጥ ገባች…የአሸናፊነት ስሜት ተሰምቷታል…

ከጓደኛዋ ጋር ወደ አንድ ዘመናዊ ሬስቶራንት ገብተው የሚፈልጉትን አዘዙ…ትንሽ በልተው ብዙ አተረፉ። ተዝናኑ። ሂሳቡ ሲመጣ ቢሉ ላይ 1420 ብር ይላል ።
ከቦርሳዋ ውስጥ 1500 ብር አውጥታ ሰጠች ። መልሱን ለሪስቶራንቱ ባለቤት ቲፕ እንዲሆነው ነግራው ወጥተው ሄዱ…

ይህ ድርጊት ለሬስቶራንቱ ባለቤት አዲስ አይደለም፣ ለእንቁላል ሻጮ ግን አስደንጋጭና ልብ ሰባሪ ነው…

➻ከድሆችና ከምስኪኖች የምንፈልገውን ለማገኘት የበላይነታችንን ለማሳየት የምንጥረው ለምንድን ነው? የእኛን እርዳታ ለማይፈልጉትስ ቸር ሆነን ለመታየት ለምን እንፈልጋለን?

ከፌስቡክ መንደር

#ሼር🙏
#ከጉሊት #ግዙ

20/08/2025

I am Born in water
I live in water
But when I get out of water and water touches me I Will die
What I am??

27/06/2025

!

ሰውየው አፈ ቅቤ ሆደ ጩቤ ነው ስንል ያለ ምክንያት አይደለም እስስት እንደምትባለው ነፍሳት በማንኛውም አጋጣሚ ከለሩን መቀያየር ይችላል ለስልጣኑ ሲል እጅግ ጨካኝ ሰው ነው። አብይ አህመድ ከውሸቱም በላይ ሃገር የመምራት ብቃት የለውም ለዚህም ትልቅ ማሳያው የሰባቱ ዓመት የቁልቁለት ጉዞ ሲሆን ከሰላም ማጣት እስከ ኪኮኖሚ ውድቀት ብሎም የፍትህ ተቋማት በነጻነት አለመንቀሳቀስን ጨምሮ ብዙ ነገሮችን መጥቀስ ይቻላል በወንጀል ደረጃ በአብይ አህመድ አገዛዝ ዘመን ያልተፈጸመ ነገር የለም ሁሉም ተፈጽሟል። ያልተፈጸመ ነገር ምንድን ነው ብለን ብንጠይቅ በጎነትና መልካምነት ብቻ መልስ ይሆናሉ ።

1. ሳናጣራ አናስርም
2.ጊዜ ስለሌለኝ ከኖቬል ሽልማት ፕሮግራም ላይ አልገኝም
3. አንዲት ፈረንሳዊ ላግባህ ብላኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ
4. በተከልነው ችግኝ የሀረማያ ሀይቅ ወደነበረበት ተመለሰ
5. ነዳጅ ማውጣት ጀምረናል
6. በእኔ ዘመን አሳዳጅና ተሳዳጅ አይኖርም
7. ወደ ትግራይ አንድ ማክስ እንጅ አንዲትጥይ ትአልክም
8. እመኑኝ አሻግራችኋለሁ
9. የኤርትራ ሰራዊት በጦርነቱ አልተሳተፈም
10. ስንዴ ኤክስፖርት ልናደርግ ነው
11. ወይዘሪት ብርቱካን ሚቅደሳ ምርጫ አይራዘምም ስላቸው ስልክ ጆሮየላ ይዘጉብኝ
12. በአፍሪካ እንደኔ ብዙ ደጋፊ ያለው መሪ የለም
13. 5 ቢሊዮን ችግኝ የአሜሪካ መንግስት ልትከል ቢል አይችልም፣ እኛ አድርገንዋል
14. እንዲህ አይነት ፋውንቴንም ሆነ አበባ ዱባይ እና ላስቬጋስ እንኳ የላቸውም
15. እያንዳንዱን የመንግስት ስብሰባበ ቀጥታ ለህዝብ እናስተላልፋል
16.በልጅነቴ እናት ቡና ግዛ ብላ ስትልከኝ መኪናየን አስነስቼ ቡርርር እያደረኩ እሄድ ነበር
17. ስሚንቶ በ600 ብርይሸጣል
18. ከኖቤል ሽልማት የኢትዮጵያ እናቶች የሚመርቁኝ ይበልጥብኛል
19. ሚዲያ ዘግቶ፣ ተፎካካሪ አስሮ፣ ሃሳብ ዘግቶ የመንደር አለቃ መኮን ይቻላል እንጅ
የሀገር መሪ መሆን አይቻልም እኔም አላደርገውም
20.ሀጫሉን ማንም ሳያውቀው ለ10ዓመት ያክል ጓደኛዬ ነበር
21.ጦርነቱን አሸንፈናል
22. ለማንና እኔን የሚለየን ሞት ነው
23. አምቦን ኒዮርክ እናደርጋታለን
24. ሱፊና ሰለፊ አብረው መስገድ የጀመሩት እኔ ከመጣሁ ነው
25. የዘይት ገብያው ተረጋግቷል
26.የወለጋ ህዝብ ውሃ ብጠይቁት ወተት የሚያጠጣ ነው
27.«ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንድካሄድ አደርጋለሁ
28. ስናጠፋ ቆንጥጡን
29. ባለፉት 2 ዓመታት በኦሮሞ ክልል ብቻ 28000 ት/ቤቶች አስገንብተናል
30.የጨረባ ምርጫን ለማስቆም መንግስት ይገደዳል
31.በ7 ዓመቴ የኢትዮጵያ ንጉስ እንደምሆን አውቅ ነበር
32. ቦንቡ ሲፈነዳ ጓደኞቼ ሞተው እኔ ብቻ ቀረሁ
33. መግደል መሸነፍ ነው
34. ሸህ አላሙዲንን ከሳውዲ አስፈትቼ አመጣቸዋለሁ
35. አሳምነውን ከእስር ያስፈታሁት እኔ ነኝ
36. በኔ ምክንያት አንድ ሰው ከሞተ ስልጣኔን እለቃሁ
37. ለማ መገርሳ ትላንት በግልፅ ዛሬ በድብቅ አለቃዬ ነው!
38. ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞ ትኢትዮጵያ
39. ጠቅላይ ሚ/ር እንደምሆን መለስ ዜናዊም ያውቁ ነበር
40. ልጅ ሁኘ በሻሻ ላይ ጓደኞቸ ጠቅላይ ሚኒስተር እንደምሆን ይነግሩኝ ነበር!
41. ተቃዋሚዎች በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ
42. የአማራ ፋኖ ከመከላከያ ጥቁር ክላሽ ቀምቷል
43. እናቶች ይፀልዩልኛል
44. አዲስ አበባ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኦሮሞ ጥላቻ አለ
45. ኦሮሞ በእኔ ስልጣን ዘመን ያለውን ተነጠቀ እንጂ እላፊ አልወሰደም
46. ኢትዮጵያ የጋዝ ምርትን ወደ ገበያ ልታቀርብ ነው። በቅርቡ የራሷን የተፈጥሮ ጋዝ ለገበያ ልታ

በጎንደር ዘመነ መንግስት የነገሱ የንጉሶች ስምና የነገሱባቸው ዓመተምህረቶች፦1.አፄ ሰርፀ ድንግል ከ1553___1587 ዓ.ም2.አፄ ያዕቆብ ከ1587___1594 ዓ.ም3.አፄ ዘድንግል ከ1594...
20/06/2025

በጎንደር ዘመነ መንግስት የነገሱ የንጉሶች ስምና የነገሱባቸው ዓመተ
ምህረቶች፦
1.አፄ ሰርፀ ድንግል ከ1553___1587 ዓ.ም
2.አፄ ያዕቆብ ከ1587___1594 ዓ.ም
3.አፄ ዘድንግል ከ1594____1595 ዓ.ም
4.አፄ ሱስንዮስ ከ1595____1623 ዓ.ም
5.አፄ ፋሲል ከ1623____1659 ዓ.ም
6.አፄ ዮሀንስ (ፃድቁ) ከ1659____1674 ዓ.ም
7.አፄ ኢያሱ ( አድያም ሰገድ) ከ1674____1698 ዓ.ም
8.አፄ ተ/ሀይማኖት (ርጉም) ከ1698____1700 ዓ.ም
9.አፄ ቴዎፍሎስ ከ1700____1703 ዓ.ም
10. አፄ ዮስጦስ ከ1703____1708 ዓ.ም
11.አፄ ዳዊት (አድባር ሰገድ ከ1708____1713 ዓ.ም
12.አፄ በካፋ (መሲህ ሰገድ) ከ1713___1722 ዓ.ም
13.አፄ ኢያሱ 2ኛ ከ1722___1747 ዓ.ም
14.አፄ ኢዮአስ ከ1747___1762 ዓ.ም
15.አፄ ዮሀንስ 2ኛ (ዘዋህድአዴሁ) ከ1762___1763 ዓ.ም
16. አፄ ተ/ሀይማኖት (መናኔ መንግስት) ከ1763___1770 ዓ.ም
17.አፄ ሰለሞን ከ1770____ 1772 ዓ.ም
18.አፄ ተ/ጊዮርጊስ (ፈፃሚ መንግስት) ከ1772____1777 ዓ.ም
ከ1777_____1847 ዓ.ም ዘመነ መሳፍንት ከዘመነ መሳፍንት በኋላ ማለትም
ከ1847____1860 አፄ ቴዎድሮስ።
# NB ፦ አመተ ምህረቶች የተፃፉት በኢትዮጵያን አቆጣጠር ነው፡፡
ስህተት ካለ ጨምሩ

☞  #በአፍሪካ የትምህርት ስርአት  #እንግሊዝኛ ቋንቋን መማር ግዴታ ሲሆን ግብርናን መማር ግን ምርጫ ነው፡፡ ለዚያም ነው እንግሊዝኛ ተናጋሪ ረሀብተኛ የሆንነው!" —  #ሮበርት ሙጋቤ☞  #...
10/06/2025

☞ #በአፍሪካ የትምህርት ስርአት #እንግሊዝኛ ቋንቋን መማር ግዴታ ሲሆን ግብርናን መማር ግን ምርጫ ነው፡፡ ለዚያም ነው እንግሊዝኛ ተናጋሪ ረሀብተኛ የሆንነው!" — #ሮበርት ሙጋቤ

☞ #አየህ #ቋንቋቸውን የሚያስተምሩህ ትእዛዛቸውን እንድትሰማ ነው። እንግሊዝኛ ቋንቋቸው ሆድህን አይሞላ፣ ረሃብህን አያስታግስ። ደግሞም እንግሊዝኛ ቋንቋ ብቻ አይደለም፤ የአውሮፓ ታሪክ፣ የምእራባውያን ፍልስፍና ወዘተ ብዙ ኮተቶችን ትማራለህ። አንድ ቁራሽ እንጀራ ለመብላት ጠቅሞህ አያውቅ። የአፍረካ ትምህርት የሚፈጥረው የተማረ ደንቆሮ ነው።

☞ #ትምህርት ኑሮን ካላሻሻለ፣ አመለካከትን ካልሞረደ፣ ተጨባጭ ለውጥ ካላመጣ ምኑን ትምህርት ሆነ። ግቢ መመረቅ፣ ጋዋን መልበስ፣ በእንግሊዝኛ የበቀቀን ዲስኩር ማድረግ አይደለም። የማህበረሰቡን ኑሮ መቀየር ነው።
ምንጭ: ሮበርት ሙገቤ

20/11/2024
16/11/2024

ክርስቲያኖ ሮናልዶ አዲስ ሪከርድ አስዝግቧል ..

ትላንት ምሽት ፖርቹጋል ፖላንድን 5 ለ 1 ባሸነፈችበት ምሽት ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን እና አንድ አሲስት ያደረገ ሲሆን ከዛ በተጨማሪ በብሄራዊ ቡድን 132 ጨዋታዎችን በማሸነፍ በሰርጂዮ ራሞስ ተይዞ የነበረዉን ሪከርድ ማሻሻል ችሏል።

Address

Abrahamgetahun09@gmail. Com
Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abrish Negn Kewubitu Dangila posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category