የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት

የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት, Grocers, Debre Birhan.

በአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ  ከደብረኤባ ቀበሌ   ነዋሪ ሴቶች ጋር "ፈተናዎችን ወደ እድል በመቀየር ህዝባችንን እናሻግራለን!" በሚል ርዕስ ሲካሄድ  የዋለዉ  ኮንፈረንስ  ተጠናቋል።የኮን...
02/06/2023

በአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ከደብረኤባ ቀበሌ ነዋሪ ሴቶች ጋር "ፈተናዎችን ወደ እድል በመቀየር ህዝባችንን እናሻግራለን!" በሚል ርዕስ ሲካሄድ የዋለዉ ኮንፈረንስ ተጠናቋል።

የኮንፈረንሱ ተሳታፊውች እንደገለጹት አሁን እንደ ክልላችን እየገጠመን ያለውን ፈተና የምንወጣበትን ስልት የመከርንበት ነው ብለዋል።

በአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ የደብረ ኤባ ቀበሌ ዋና አስተዳደር አቶ ጋሻዉ ከበደ እንደተናገሩት ያሉብንን የአስተሳሰብ መዛባቶች አርመን ክልላችንን ወደ ፍጹም ሰላም ለማምጣት ሁላችሁም የየራሳችሁን አስተዋፀኦ ልታደርጉ ይገባል ብለዋል።

የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ሴቶች አማካሪ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ብርሃኔ ስዩም በበኩላችው አማራ በኢትዮጵያ የመንግስታት ታሪክ ውስጥ ሰፊ እና አይረሴ ታሪክ ሰርተው አልፈዋል እኛም የአባቶቻችንን እና የእናቶቻችን ፈለግ በመከተል የጽንፈኞችን አማራን የመበታተን አላማ አክሽፈን ትልቅነታችን ማስመስከር አለብን በተጨማሪም የአማራ ክልል የዘመናት ጥያቄ ለመፍታት የትግል ስልታችን በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ዉስጥ ሆኖ ጠንካራ እና ፅናትን የተላበሰ አማራጭ በመከተል ሊሆን እንደሚገባ በአፅኖት ተናግረዋል።

28/02/2023
የአፄ ዘርያዕቆብ ክፍለ ከተማ በሴቶች አማካሪ አዘጋጅነት የሴቶች ፎረም ተካሄደ።ጥቅምት 14/2015ዓ.ምበፎረሙ ላይ የደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ  ኃላፊ ወ...
25/10/2022

የአፄ ዘርያዕቆብ ክፍለ ከተማ በሴቶች አማካሪ አዘጋጅነት የሴቶች ፎረም ተካሄደ።
ጥቅምት 14/2015ዓ.ም
በፎረሙ ላይ የደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ የለምሸዋ በቀለ፣የደ/ብርሃን ከተማ ሴ/ህ/ማ/ጉ/መ ኃላፊ ወ/ሮ በለጥሽ ግርማ፣ የደ/ብርሃን ከተማ ሴቶች ሊግ ኃላፊ ወ/ሮ ራሄል አስራት፣ የደ/ብርሃን ከተማ ሴቶች ሊግ ም/ኃላፊ ወ/ሪት ብዙአየሁ ደሳለኝ፣ የደ/ብርሃን ከተማ የበጎ ሰው አምባሰደር ወ/ሮ ክርስቲና አበራ፣ የአፄ ዘርያዕቆብ ክፍለ ከተማ ሴት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የቀበሌ አመራሮችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በፎረሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ የለምሸዋ በቀለ በንግግራቸው ሴቶች በአመራርና ውሳኔ ሰጭነት እኩል ተሳታፊ እንዲሆኑና በሁሉም የልማት ዘርፎች እና የስልጣን ዕርከኖች አርአያ የሆኑ የሴት አመራሮችን ለማፍራት ታስቦ የተደራጀ ሲሆን የሴት አመራሮች እርስበርስ የምትደጋገፉበት ልምድ የምትለዋወጡበት እና ያጋጠሙ ችግሮችን ተነጋግራችሁ የምትፈቱበት መድረክ መሆን አለበት ሲሉ ገልፀዋል።በፎረሙ የአፄ ዘርያዕቆብ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊወ/ሮ ፅጌ ታዬ አመራር ምንድነው የአመራር ባህሪያት የአመራር አይነቶች እና የሴት አመራሮች ባህሪያት ፅሁፍ ላይ ገለፃ አድርገው የመወያያ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የሴት አመራሮች በአግባቡ ባለመደራጀታቸዉ በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ ልማት ዘርፍ እኩል ተጠቃሚ አልነበሩም የሚሉት ወ/ሮ/ፅጌ ታዬ ጥቂት ጊዜያት በተሰራው ስራ ሴቶች በየትኛውም መስክ ተግባራትን በግንባር ቀደምትነት መፈፀም የቻሉ በመሆኑ የፎረሙ መመስረት ትልቅ ጉልበት ይኖረዋል ሲሉ ገልፀዋል።
ተሳታፊዎችም የሴቶችን ብቃት ከቤት ጀምሮ ማሳደግ አለብን ፣ ሴቶች ወደፊት እንዲመጡ የሴት አመራሮች ድርሻ የጎላ ነው ፣ በየደረጃው ያሉ ሴቶች እችላለሁ በሚል መንፈስ አንድነታቸውን አጠናክረው መስራት አለባቸው ተሳትፏችን በውይይት ብቻ ሳይሆን የአካባቢያችንን ፅዳትና ውበት በመጠበቅ እና ረዳት ለሌላቸውን ሀረጋውያንን በማገዝና በመደገፍ ሊሆን ይገባል የሚሉ ሃሳቦችን አንስተዋል፡፡
በመጨረሻም የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የአደርጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ዘሪቱ አስራት የአፄዘርያዕቆብ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፅጌ ታዬ የደብረብርሃን ከተማ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ በለጥሽ ግርማ የተነሳው ሃሳብ ገዢ መሆኑን አስቀምጠው በበጀት አመቱ አደረጃጀቶችን አጠናክሮ መስራት ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ፎርሙ መቋቋም ብቻ ሳይሆን ውጤት የሚያመጣና በእርግጥም ሴቶች ብቁና ውሳኔ ሰጪ እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ እንዲሁም አስተሳሰቦች ላይ ከቤት ጀምሮ መስራትና ሴቶችን ለለውጥ ዝግጁ ማድረግ ድርብ ኃላፊነት አለብን፡፡ በየደጃው የግልፀኝነት ተጠያቂነትና ፍትሃዊ አሰራሮች እንዳዲሰፍኑ የሴቶችን ሚና ማጉላት ይጠበቃል የተሻለ ተግባር የፈፀሙ ሴቶችን ማበረታታት እና እውቅና መስጠት አለብን።ባለንበት ቦታ እና በተሰማራንበት የስራ መስክ ውጤታማ መሆን አለብን የሚሉ ሀሳቦች ቀርበው መግባባት በመፍጠር ውይይቱ ተጠናቋል።
"የሴቶትን የመሪነት አቅም በመጠቀም ሁለንተናዊ ብልፅግናን እናረጋግጣለን።"

Address

Debre Birhan

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category