13/12/2023
ሀምባሪቾን ወደ ክብሩ መልሱት‼️
ተራራ የሆነ ስም ተሸክሞ ትልቅ ህዝብ ወክሎ ከፕሪሚየር ሊጉ መቀላቀል ቻለ፡፡ስሙን የሚያክል ድጋፍ፣ለክብሩ የሚጨነቅ ደጋፊ ባለቤት መሆኑን ለማስመስከር ሁለት የመጀመሪያዎቹ ፍልሚያዎች በቂ ነበሩ፡፡
ግን ከዚያ በኃላ ለምን ቡዳ በላው‼️
ሀምባሪቾ አሁን ከፕሪሚየር ሊጉ የደረጃ ሠንጠረዥ ግርጌ ሻሸመኔ ከተማ ብቻ በልጦ በሁለት ነጥብ የአዳማ ቆይታውን ለማጠናቀቅ ተቃርቧል፡፡የክለቡ ተከታታይ ሽንፈትና ውጤት ማጣት ደጋፊውን ክፉኛ አሳዝኗል፡፡ከዚህ በመነሳት በክለቡ ላይ መሠረታዊ ለውጥ መደረግ እንደለበት ጥያቄዎች ሲቀርቡ ሰንብተዋል፡፡
ለዚህ ጥያቄና መልስ የሚሰጥ፣ለክለቡ ውጤት ማጣት ኃላፊነት የሚወስድ ቆራጥ፣ህዝብን የሚወግናና ለእውነት የቆመ አካል ግን እስካሁን አልተገኘም፡፡አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ለተወሰኑ ተጨዋችች ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደተሰጣቸው፣ለአሰልጣኙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጠውና በአጋማሽ ላይ ተከላካይና አጥቂ ለመግዛት ከውሳኔ ተደርሷል፡፡
ውሳኔው እንዲሁ በግርድፉ መልካም ነው እንበል፡፡ነገር ግን ክለቡ ያለበትን ችግር የሚፈታ፣የሚመሩ አካላትም ችግሩን በውል የተገነዘቡ አይመስለኝም፡፡የክለቡን ህሊውና ከማስጠበቅና የደጋፊውን ሞራል ከመጠበቅ ብሎም የህቡን ፍላጎት ከማክበር ይልቅ ለግለሰቦች የተጨነቁ፣እንዳይነኩባቸው የሳሱ ይመስላል፡፡
በየትኛውም ዓለም በተከታታይ ውጤት ያጣ፣የተሸነፈ፣መሻሻል ማሳየት ያልቻለ አሰልጣኝ ወይ በራሱ ፈቃድ ይለቃል ካልሆነም በቀጠረው አካል ይሰናበታል፡፡ሀምባሪቾ ከዚህ እውነት በተፀራሪ ለመቆም የሚያበቃው ምክንያት ምን ይሆን!!ዛሬ ላይ ፈጣን እርምጃ ወስዶ የክለቡን ቀጣይ ቆይታ ከማደላደል ይልቅ የይምሰል ውሳኔ መወሰን ለምን አስፈለገ!! ቦርዱና የዞኑ አስተዳደር ውግንናው ለማነው!!
እኔ ግን እን አንድ ደጋፊ እላለሁ ክለቡ መቀጠል ካለበት አሰልጣኙ ኃላፊነት ወስዶ ከዚህ ቀደም ለሠራው ሥራ ተመስግኖ በራሱ ፈቃድ መልቀቅ አለበት፡፡ይህንን ተሞክሮ ለመቅሰም ሌላ ቦታ መሄድ ሳያስፈል ተመሳሳይ ታሪክ የሚጋራውን የሻሸመኔ ከተማን መመልከት በቂ ነው፡፡ሀዲያ ሆሳዕና፣ሲዳማ ቡና እና ሌሎች ክለቦች የወሰኑትን ውሳኔ መፈተሸ ተገቢ ነው፡፡የዞኑ አስተዳደርና ቦርዱ ግን ቆም ብለዉ ራሳቸውን ይፈትሹ፡፡ኃላፊነት መውሰድ ባለባቸው ጉዳይ ሳያወላዱ ኃላፊነት ይውሰዱ፡፡ክለቡ የቴክኒክ ኮሚቴ እንዳይኖረው ለምን እንደተደረገ ይግለፅ፡፡የክለቡ አደረጃጀት እንዲስተካከል፣ጠንካራ የደጋፊ ማህበር እንዳይኖርና እንዳይመሰረት ለምን ተፈለገ??
እጃችሁን ከክለቡ ላይ አንሱ!!
ደስታችንን አትንጠቁ‼️
ሀምባሪቾን ወደ ክብሩ መልሱ‼️
አዲስ አሰልጣኝ ያስፈልገናል‼️