13/06/2024
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ባለፉት ወራት ውሰጥ የወረዳችንን ብሎም የከተማችንን ፅዳት እና ውበት ለማስጠበቅ በርካታ ተግባራት መከናወናቸው ተገለፀ
የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ድሪባ በባለፉት 10 ወራት የከተማችንን ውበት እና ፅዳት ለማስጠበቅ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ለመረጃ ክፍላችን በነበረን ቆይታ እንደሚከተለው ገልፀውልናል ።
የህዝብ ተሳትፎና ግንዛቤ ከማሳደግ ጋር በተያያዘ በወረዳችን ውሰጥ 5825 አባ ወራዎችና እማወራዎች ቤት ለቤት ግንዛቤ በስታንዳርዱ መሰረት መስጠት መቻሉን ገልፀዋል ።ከዚህ በተጨማሪም
በየሳምንቱ ሳምንታዊ የጽዳት ንቅናቄ በ8ቱም ቀጠናና በ40ዎች ብሎክ ላይ የፅዳት ንቅናቄ መካሄዱንም አብራርተዋል
ሳምንታዊ የተቋማት ጽዳት ንቅናቄ በተመለከተ አርብ አርብ በ16 ተቋማት በተለይ የወረዳ አስተዳደር 1 ፣ የትምህርት ተቋማት12 ፣ የሀይማኖት ተቋማት 4 በድምሩ በ16 ተቋማት ላይ ከፍተኛ ንቅናቄ ማድረግ ተችሏል
ሞዴል ብሎክ እና መንደር ከመፍጠር ጋር በተያያዘ በወረዳችን ከአሉን
40 ብሎኮች ውሰጥ 18 ነባር ሞዴል ብሎክ ማሰቀጠል 6 ደግሞ አዲስ ሞዴል ብሎክ መፍጠር እንደተቻለ አክለው አብራርተዋል
ከሀብት አሰባሰብ ጋር በተያያዘ 346000 ብር የሚገመት ለፅዳት ስራችን አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች በተለይ አካፋ፣ማዳበሪያ ፣ ጓንት፣ መጥረጊያ ፣ ዲስትቢን ከባላሃብቶች እና ተቋማት መሰብሰብ ተችሏል
ከደረቅ ቆሻሻ አሰባሰብ እና አገልግሎት ከመስጠት አንጻር
በወረዳችን በ40ዎች ብሎክ ያሉ እማወራ እና እባወራ በሳምንት ውሰጥ ከ2 እስከ 3 ጊዜ የቤት ለቤት አገልግሎት እንዲያገኙ ጠንካራ ስራ ተሰርቷል
በ10 ወራት ውስጥ 4600 ቶን ደረቅ ቆሻሻ በመሰብስብ 69,840,560 ብር ገቢ ማግኘት እንደተቻለ ገልፀዋል።
ከመንገድ ፅዳት ጋር በተያያዘ 14 ኪሎ ሜትር ስታንደርድ የወጣላቸው የአስፋልት መንገድ በቀን ሁለት(2) ጊዜ መጽዳት ተችሏል
የመልሶ መጠቀምና ዑዳት ማድረግ በተመለከተ በህብረት ሽርክና የተደራጁት ማህበር በተለይ ማዳበሪያ ፣ብረታ ብረት፣ ሀይላንድ፣ማይካ፣ጠርሙሶች እና የወረቀትና ካርቶን ዑደት በማድረግ 10,000,000 ብር በላይ ማግኘት እንደተቻለ ገልፀዋል።
ህግ ወጥ ቆሻሻ በሚጥሉ የግልና የመንግስት ተቋማት ላይ በአዋጅ 150/2015 የእርምት እርምጃ በመውሰድ ብር 65,000 ብር ገቢ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል ።
05/10/2016 ዓ.ም