Hadiya ከቤራ

Hadiya ከቤራ kabea🐆 ✅⚫⚪🔴★ ሆ ..ሳ..ዕ..ና 🇪🇹

  ከክለባችን ሃዲያ ሆሳዕና ስለነበረህ ጊዜ ከልብ እናመሰግናለን🙏💥አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ በትልቁ የሚታወቅ ስም ነው። በተለይም ከሆሳዕና ከነማ ጋር ባሳለፈው ጊዜ ...
11/08/2025


ከክለባችን ሃዲያ ሆሳዕና ስለነበረህ ጊዜ ከልብ እናመሰግናለን🙏
💥አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ በትልቁ የሚታወቅ ስም ነው። በተለይም ከሆሳዕና ከነማ ጋር ባሳለፈው ጊዜ በስፋት ይታወቃል።

ስኬቶች እና አበርክቶዎች:
💥አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ የሆሳዕና ከነማ ዋና አሰልጣኝ ሆነው ቡድኑን #ሁለቴ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በማሳደግ በክለቡ ታሪክ የማይረሳ ስራ ሰርተዋል።
* በ2007 ዓ.ም ሆሳዕና ከነማን ከሀላባ ከነማ ጋር ባደረጉት የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በማሸነፍ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጉን ሲያረጋግጡ የቡድኑ መሪ ነበሩ።
በተጨማሪ 2011 ሃዲያ ሆሳዕና ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አሳድገዋል። በፕሪሚየር ሊጉም 2008,2012,2016,2017 ዓ/ምህረቶች ከክለባችን ሃዲያ ሆሳዕና ጋር ቆይተዋል። የብሔራዊ ሊግ ዋንጫ ሁለቴ የአዲስአበባ ከተማ ዋንጫ አንዴ በማንሳት የመጀመሪያው ነው።

💥አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ(መንቾ) ለሆሳዕና ከተማ ከመጫወት አንስቶ ሃዲያ ሆሳዕና እስከማሰልጠን ክለቡ በሚፈልቸው ወቅት ሁሉ ክለቡን በመቀላቀል ሙያዊ አገልግሎት የሰጡም ናቸው

💥 እርሳቸው እንደሚሉት፣ የቡድናቸው የስኬት ምስጢር በኳስ ቁጥጥር ላይ የተመሰረተ አጨዋወት መከተላቸው እና የተጫዋቾች ተነሳሽነት ነው።

💥 በክለባችን ላገለገሉበት ጊዜ ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን። በክለቡ በቆዩበት ጊዜ ቡድናችንን
በ የእርስዎ ትጋት፣ ሙያዊነት እና ለቡድናችን ያለዎት ፍቅር ሁሌም ይታወሳል ከእርስዎ ጋር ክለባችን ያሳለፍቸው ጊዜያት እና ያገኘናቸው ድሎች ሁልጊዜም በልባችን ይኖራሉ።
በቀጣይ ላይ ታላቅ ስኬትን እና ደስታን እንመኝልዎታለን። መልካም እድል!"
✍️ናኒ የከቤራው

የካሌብ በየነ ቀጣይ ማረፊያ የት ሊሆን ይችላል ?በ2013 ዓ/ም ከሀዲያ ሆሳዕና ወጣት ቡድን ወደ ዋናው ቡድን በማደግ ለሶስት ተከታታይ ዓመታት በግራ መስመር ተከላካይና የመስመር አጥቂ ቦታ ...
10/08/2025

የካሌብ በየነ ቀጣይ ማረፊያ የት ሊሆን ይችላል ?

በ2013 ዓ/ም ከሀዲያ ሆሳዕና ወጣት ቡድን ወደ ዋናው ቡድን በማደግ ለሶስት ተከታታይ ዓመታት በግራ መስመር ተከላካይና የመስመር አጥቂ ቦታ ላይ ድንቅ ብቃቱን በማሳየት በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በአንድ ዓመት ውል ወደ አርባምንጭ ከተማ በማምራት ጥሩ የውድድር ዓመት ያሳለፈው ካሌብ በየነ ከአርባምንጭ ከተማ ጋር ያለው ውል ሰኔ 30 መጠናቀቁን ተከትሎ አርባምንጭን ከተማን ጨምሮ አራት የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ተጨዋቹን የግላቸው ሊያደርጉት ከፍተኛ ፉክክር ላይ የገቡ ሲሆኑ ፤ ተጨዋቹም በጥቂት ቀናት ውስጥ አንዳቸውን ሊቀላቀል እንደሚችል ያገኘውት መረጃ ያሳያል ።

[ታሪኩ አበራ]

በፌዴራል፣ በአዲስ አበባ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልና በሀዲያ ዞን የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከዚህ ቀደም ዞኑን በዋና አስተዳዳሪነት የመሩ አመራሮች በሀዲያ ልማትና መልካም አስተዳደ...
15/07/2025

በፌዴራል፣ በአዲስ አበባ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልና በሀዲያ ዞን የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከዚህ ቀደም ዞኑን በዋና አስተዳዳሪነት የመሩ አመራሮች በሀዲያ ልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ምክክር አካሄዱ፤

ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም (ሆሳዕና) በፌዴራል፣ በአዲስ አበባ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልና በሀዲያ ዞን የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ከዚህ ቀደም ዞኑን በዋና አስተዳዳሪነት የመሩ አመራሮች በሀዲያ ልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ የምክክር አካሄደዋል።

መድረኩ በተመሳሳይ በዞኑ ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች ጋር ስኬታማ ምክክር መደረጉ የሚታወስ ሲሆን፤

በዛሬውም መድረክ ከዚህ ቀደም በዞኑ ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረቶች ጋር የተካሄዱ የምክክር መድረኮች የአፈፃፀም ሪፓርት ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን፤ የቀጣይ የማጠቃለያ ኮንፍረንስ መድረክ ዕቅድ ተገምግሞ መድረኩ በስኬት ተጠናቋል።

Address

Adis Abab
Vikravandi
1234

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya ከቤራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category