Taytu ጣይቱ

Taytu ጣይቱ Informazioni di contatto, mappa e indicazioni stradali, modulo di contatto, orari di apertura, servizi, valutazioni, foto, video e annunci di Taytu ጣይቱ, Negozio di alimentari, sweedn, Rome.

የከሸፈው ፕሮፖጋንዳ! ወያኔ ሰሜን እዝን አጥቅቶ ኢትዮጵያን ሲወርር ከጦርነቱ ባልተናነሰ መጠነ ሠፊ ፕሮፖጋንዳ ከፍቶም ነበር። ግን ከመቀጥቀጥ እና ከመሸነፍ ሊታደገው አልቻለም። የኢትዮጵያ ጀ...
17/10/2025

የከሸፈው ፕሮፖጋንዳ!

ወያኔ ሰሜን እዝን አጥቅቶ ኢትዮጵያን ሲወርር ከጦርነቱ ባልተናነሰ መጠነ ሠፊ ፕሮፖጋንዳ ከፍቶም ነበር። ግን ከመቀጥቀጥ እና ከመሸነፍ ሊታደገው አልቻለም። የኢትዮጵያ ጀግኖች ቀጥቅጠው እርቃኑን አስቀርተው የሽንፈት ውርደትን አልብሰው አሸነፉት።

ዛሬም የከሸፈ ፕሮፖጋንዳውን አንግቦ እዚህም እዚያም የሚተነኩሰው ጽንፈኛው ኀይል ከባድ ምት እየደረሰበት ለቅሶ ላይ ይገኛል።

ነጭ ውሸት በፀራራ ፀሀይ!
ታዲያ ለደጋፊዎቹ እጅ መንሻ ይዞ የቀረበው አንዲት ታጣቂ አባሉን በጥምር ጦሩ ምት ሲያጣት ልዩ የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ማዋልን መርጧል። በአስከሬን መነገድ የቆየ ልማዱ ቢሆንም ዛሬም ብዙ ውሸት እና ሰፊ የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻን እንደ ግብ ቆጥሮ እያስተጋባ ተስተውሏል። ግን ውሸት ውሸት እንጅ እውነት ሆኖ አያውቅም!

የምስጉን ስነምግባር እና ጀግንነት ተምሳሌቱን የመንግስት ጦር በዚህ አይነት ፕሮፖጋንዳ ስሙን ማጠልሸት ተቀባይነት የሌለው የተሸናፊው ጽንፈኛ ቡድን ባህሪ መሆኑን ሁሉም ተረድቶታል።

ጀግኖቻችን የከሸፈውን ፕሮፖጋንዳ ወደኋላ እየተው ወደፊት በደማቅ ድል ታጅበው ጉዟቸውን ቀጥለዋል!

አዲስ ትርክት ማዋለድ-የጽንፈኛዉ አዲሱ ማደናገሪያ፤ ሕወሓት ገና ከጽንሰቱ ጀምሮ ከመስመሬ ወጣችሗል በሚል የራሱን የቡድን አባላት ረሽኖ በስማቸዉ ግን የዘመቻ ስያሜ ይሰጣቸዉ ነበር። ከዛም ፊ...
17/10/2025

አዲስ ትርክት ማዋለድ-የጽንፈኛዉ አዲሱ ማደናገሪያ፤

ሕወሓት ገና ከጽንሰቱ ጀምሮ ከመስመሬ ወጣችሗል በሚል የራሱን የቡድን አባላት ረሽኖ በስማቸዉ ግን የዘመቻ ስያሜ ይሰጣቸዉ ነበር። ከዛም ፊት አሰልፎ የሚደመሰሱትን አሟሟታቸዉን ለሰራዊቱ እና ለህዝቡ አዲስ ትርክ እየፈጠረ ያነሳሳባቸዉ ነበር።

ይሄ ብቻ አይደለም ሀዉዜን ላይ የአካባቢውን ህዝብ በጅምላ ራሱ ጨርሶ "በጠላት የዘር ጭፍጨፋ ተፈጸመ" ብለዉ ህዝብ ያነሳሱበት የሚረሳ ታሪክ አይደለም።

ከሰሞኑ ከህወሓት እና ከሻብያ ተልዕኮ ተቀብሎ በተለያዩ አካባቢዎች ትንኮሳ የፈጸመዉ ጽንፈኛ ቡድን እንደቅጠል እየረገፈ የተረፉትም መዉጫና እና መግቢያዉ ጠፍቶባቸዉ በፍርሃት እና በጭንቀት እየተናጡ እንደሆነ ከዉስጥ ምንጮች ማረጋገጥ ችያለሁ።

አጣብቂኝ ዉስጥ የገባዉ ይህ ቡድን ከትግል መምህሩ ከወያኔ እና ሻብያ የወረሰዉን አዲስ ትርክ ማዋለድ እንደ መዉጫ መንገድ እየተጠቀመዉ መሆኑን ሳይ ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር እንዲሉ አፍሬባቸዋለሁ።

ከሰሞኑም አንዲት የጽንፈኛዉ አባል የነበረች "ባለም" የተባለች አባላቸዉ ከሌሎች ግብረ አበሮቿ ጋር ባደረገችዉ ትንኮሳ ተደምስሰዋል።

የደረሰበትን ምት መቋቋም ያቃተዉ ጽንፈኛ ቡድን በአሁኑ ለተደመሰሰችዉ አጋራቸዉ አዲስ ትርክ ፈጥረዉ በፍርሀት እና በጭንቀት እየተናጠ የሚገኘዉን አባላቸዉን እያነሳሱ እንደሆነ እያየን ነዉ። ይሄዉ ተግባራቸዉም ለትህነግና ለሻብያ ማጋዣ ሁነዉ እያገለገሉ መሆናቸዉ ማሳያ ምስክ ነዉ።

የህወሓት እና የሻብያ ተልዕኮ የት ያደርሳችሁ ይሆን እናያለን!

እውነት በፈጠራ ፖሮፖጋንዳ ዘመቻ አትዳፈንም! የሰላም አማራጭን መግፋትም ከጠንካራ ክንዶች ምት አያድንም! የሰላም አማራጭን ገፍቶ የአማራን እናት ማጀት እያራቆቱ፣ ሠርቶና ለፍቶ አዳሪውን ሕዝ...
17/10/2025

እውነት በፈጠራ ፖሮፖጋንዳ ዘመቻ አትዳፈንም!

የሰላም አማራጭን መግፋትም ከጠንካራ ክንዶች ምት አያድንም!

የሰላም አማራጭን ገፍቶ የአማራን እናት ማጀት እያራቆቱ፣ ሠርቶና ለፍቶ አዳሪውን ሕዝብ እየዘረፉ፣ አማራን ለታሪካዊ ጠላቶቹ አሳልፎ ለመስጠት በባዳነት እየሰሩ የሕዝብ ተቆርቋሪ መምሰልአይንን ያለፈበት ቁማር ነው። ጽንፈኛና ባንዳ በጀግናው መከላከያ ሠራዊትና በአማራ የጸጥታ ሀይል ከገባሽበት እየገባ አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣሽ በበሬ ወለደ የተለመደ የፈጠራ ዘመቻ ጥሩባ መንፋት የተሰለቸ ልማድ ነው።

ሕዝብም የባንዳና የጽንፈኛን የፈጠራ ፕሮፖጋንዳ ጠንቅቆ ካወቀው ውሎ አድሯል። ጠንካራ የሕዝብ ክንዶች አማራን ከጠላቶቹ በላይ የዘረፈውን፣ የገደለውን፣ ያሰቃየውን ጽንፈኛ ቡድን ከተወተፈበት እየመዘዙ፣ ከገባበት እየገቡ መደምሰሱን ይቀጥላሉ።
በጡት የፖለቲካ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ የሚለወጥ የለም። ቻለው እንግዲህ!!!

09/10/2025
09/10/2025

የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዲኖሩ ለመቀበል ዝግጁ ነን፤

ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ደምለው እና የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሰጡት ማብራሪያ፤ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ከዞኑ የተፈናቀሉና ያልተመለሱ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚቀበሏቸው ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ህይወታቸውን እየመሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የአማራና የትግራይ ህዝብ ለዘመናት አብረው የኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሰሜኑ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት ብዙዎች በኖሩበት አካባቢ እየኖሩ መሆኑን አስታውሰው፤ በወቅቱ ተደናግጠው ከሄዱት መካከል ደግሞ ወደ ዞኑ ተመልሰው ሰላማዊ ህይወት መምራት የጀመሩ መኖራቸውን ተናግረዋል።

ምክትል ዋና አስተዳዳሪው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በበኩላቸው እንደገለጹት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው መመለስ አለባቸው።

በአካባቢው ሰላም ለመፍጠር አንድን ማህበረሰብ አፈናቅለህ አንዱን ማኖር የሚቻል አይመስለኝም ብለዋል።

ምክትል ዋና አስተዳዳሪው፤ የተፈናቃዮች ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝ በሁሉም በኩል ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።

መንግስት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በተከታታይ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውንና ጥረቶች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል ሲል የገበዉ ኢዜአ ነዉ።

09/10/2025

የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዲኖሩ ለመቀበል ዝግጁ ነን።

ባሕር ዳር: መስከረም 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሸተ ደምለው እና የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሰጡት ማብራሪያ፤ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የዞኑ ዋና አሥተዳዳሪ ከዞኑ የተፈናቀሉና ያልተመለሱ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚቀበሏቸው ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ህይወታቸውን እየመሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የአማራና የትግራይ ሕዝብ ለዘመናት አብረው የኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሰሜኑ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት ብዙዎች በኖሩበት አካባቢ እየኖሩ መሆኑን አስታውሰው፤ በወቅቱ ተደናግጠው ከሄዱት መካከል ደግሞ ወደ ዞኑ ተመልሰው ሰላማዊ ህይወት መምራት የጀመሩ መኖራቸውን ተናግረዋል።

ምክትል ዋና አሥተዳዳሪው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በበኩላቸው ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው መመለስ አለባቸው ብለዋል።

በአካባቢው ሰላም ለመፍጠር አንድን ማኅበረሰብ አፈናቅለህ አንዱን ማኖር አይገባም ብለዋል።

ምክትል ዋና አሥተዳዳሪው፤ የተፈናቃዮች ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝ በሁሉም በኩል ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።

መንግሥት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በተከታታይ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውንና ጥረቶች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

ገጥሞ የምን ለቅሶ! የአማራን ህዝብ ሊዘርፍ፣ ሊሰርቅ፣ ሊያግትና ልጆቹን ከትምህርት ገበታ በመስተጓጐል ስልጣን ላይ ሊወጣ ጫካ የገባ ጽንፈኛ ቡድን ግብሬን በአደባባይ ለህዝብ አጋለጡብኝ በሚል...
07/10/2025

ገጥሞ የምን ለቅሶ!

የአማራን ህዝብ ሊዘርፍ፣ ሊሰርቅ፣ ሊያግትና ልጆቹን ከትምህርት ገበታ በመስተጓጐል ስልጣን ላይ ሊወጣ ጫካ የገባ ጽንፈኛ ቡድን ግብሬን በአደባባይ ለህዝብ አጋለጡብኝ በሚል በየሚዲያው ሲያለቅስ እያየን ነዉ።

ለነገሩ አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል እንዲሉ ዘዉ ብለዉ ፎቶ ለመነሳት በገቡበት አካባቢ ሁሉ መዉጣት ህልም ሁኖባቸዉ እንደጉም ተነዉ እየቀሩ ስለሆነ የዛ ስሜት እንደሚሆን አልጠራጠርም።

የጽንፈኛዉ የሚዲያ ክንፍ የሆኑት ሙሉጌታ አንበርብርና አሳየ ደርቤ የተባሉ ቅጥረኞች የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለህዝብ ግብራችን አጋለጠ በሚል "ታመን አደርን" ሲሉ አይቸ ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር እንዲሉ አፍሬያለሁ።

ሰዉየዉ እንደሆኑ ቆፍጣና ታታሪ መሪ ናቸዉ፤ ብረትን እንደጋለ መቀጥቀጥ ይችሉበታል።

አንተ የተለያየ የዳቦ ስም እየሰጠህ የሚመራዉን ህዝብ ለጉስቁልና እየዳረክ የመላእክት ስም ያዉጣልህ ወይ!?

እኛም እንላለን!
👉ሌባማ ሌባ ነዉ!
ባንዳም ባንዳ ነዉ!
ባዳም ባዳ ነዉ!
ጽንፈኛም ያዉ ጽንፈኛ ነዉ! 👈

በስምህ ሲጠራህ አቤት ማለትህ ተፈጥሯዊ ነዉ። ከሰሞኑ የጽንፈኛዉ የማህበራዊ ሚዲያ ክንፍ ያሰማራቸዉ ባንዳዎችና ያዘዙን ባዳዎች ባደባባይ ስማቸዉ ከእነ ግብራቸው ተነገረ ብለዉ "ታመምን" እያሉ...
07/10/2025

በስምህ ሲጠራህ አቤት ማለትህ ተፈጥሯዊ ነዉ።

ከሰሞኑ የጽንፈኛዉ የማህበራዊ ሚዲያ ክንፍ ያሰማራቸዉ ባንዳዎችና ያዘዙን ባዳዎች ባደባባይ ስማቸዉ ከእነ ግብራቸው ተነገረ ብለዉ "ታመምን" እያሉ ነዉ።

መሪ እንደመሪ ሌባን ሌባ፣ ባንዳን ባንዳ፣ ባዳን ባዳ ማለት ካልቻለ ምኑን መሪ ሆነዉ።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህም ያደረጉት ለህዝባቸዉ የሚመጥነዉን እንጅ ለአጥፊዎች የሚጠቅመዉን አይደለም።

ወዳጀ ሰዉየዉ ንግግራቸዉም ሆነ ግብራቸዉ ለባንዳና ለባዳ አይመችም።

ለዚህ ነዉ ስታዩት የሚያዞራችሁ፣ ስተሰሙት የሚያማችሁ!

ጽንፈኛዉ ቡድን ተሞክሮ የከሸፈዉን የትህነግ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በራሱ ህዝብ ላይ ሞክሮት እንደ እሳት ራት በገባበት ቀልጦ ቀርቷል። ከሰሞኑ ጽንፈኛው ቡድን መካነሰላም እና አካባቢዉ ፎቶ ተነስ...
04/10/2025

ጽንፈኛዉ ቡድን ተሞክሮ የከሸፈዉን የትህነግ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በራሱ ህዝብ ላይ ሞክሮት እንደ እሳት ራት በገባበት ቀልጦ ቀርቷል።

ከሰሞኑ ጽንፈኛው ቡድን መካነሰላም እና አካባቢዉ ፎቶ ተነስቶ ለቀጣሪዎቹ እና ለማህበራዊ ሚዲያ ክንፉ ለመላክ ሰተት ብሎ ገብቶ ነበር። እንደገባም በፍቅርና በአንድነት በሃይማኖት ሳይለያይ ሰዉነት ብቻ በሚያኖረው የወሎ ህዝብ መካከል የሃይማኖት ግጭት ለማስነሳት መስጅድ ዉስጥ ገብቶ አማኞች ላይ ተኩሶ ገድሏል።

ይሄን ድርጊቱን በመንግስት እና በሌሎች የሃይማኖት ተከታዮች እንደተደረገ ለማስመሰል ሞክሮ ከሽፎበታል።

ቡድኑም በቅርብ ወልድያ እና አካባቢዉ እንደሆነዉ ሁሉ የመካነ ሰላም ህዝብ በነቂስ ወጦ ባሉበት እየጠቆመ ከገቡበት ገብቶ አዉጥቷቸዋል። የመካነ ሰላም ምድርም እነሱ እንዳሰቡት ሳይሆን የረገጡት ሁሉ እንደ እሳት አቃጥሏቸዉ ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፉ ቀርተዋል። በህይወት የተረፉትም ለመንግሥት እጃቸዉን ሰጠዋል።

የመካነሰላም ህዝብም በማይመጣ መጣችሁ ብሎ በገቡበት እየገባ እያሳደዳቸዉ ነዉ።

እዉነት ተደብቆ አይቀርም!

መስቀል በወልድያ ተከበረ!!
26/09/2025

መስቀል በወልድያ ተከበረ!!

Check out Amhara Media Corporation’s video.

01/09/2025

የአማራ ክልል ርዕሠ መስተዳድር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ ለሁሉም የዞን አስተዳደሪዎች እና የከተማ ከንቲባዎች "የጎርጎራ ቃልኪዳን" ሠነዱን (የአሻጋሪ እድገትና የዘላቂ ልማት ፍኖተካርታውን) ሲያስረክቡ በምስል።

 #ትምህርት
29/08/2025

#ትምህርት

"ተማሪዎች እንዲመዘገቡ የተጀመረው ንቅናቄ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት" መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር)

ባሕር ዳር: ነሐሴ 23/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን የትምህርት ምዝገባ አስመልክተው ከሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን ባለሙያዎች እና መሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ የሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን መዋቅሩ ተማሪዎች እንዲመዘገቡ እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ የሚደነቅ መኾኑን አንስተዋል።

ቢሮ ኀላፊው ሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን በትኩረት ሲሠራ ብዙ ጉዳዮችን ይቀይራል፤ ቀይሯልም ነው ያሉት። የትምህርት ጉዳይ ልዩ አጀንዳ መኾኑንም ተናግረዋል። በተሠራው ሥራ ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት። ትምህርት ላይ የተቃጣ ጥቃት ትውልድን እንደሚጎዳም ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ በትምህርት ላይ የደረሰው ስብራት እንዲጠገን እና ልጆቹ እንዲማሩለት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለውም ገልጸዋል።

የትምህርት ሥራ የሁሉንም ድጋፍ ይፈልጋል ያሉት ኀላፊው የአማራ ክልል በትምህርት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት ቆይቷል፤ ከጉዳቱ እንዲያገግምም በጋራ መሥራት ይገባል ነው ያሉት። ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ውጭ ማድረግ ትውልድን ማምከን ነው፣ ይህን በመረዳት መሥራት ይገባል ብለዋል።

ትምህርት የሕልውና ጉዳይ ነው፤ ለሕልውና ደግሞ በትኩረት መሥራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት። አያሌ ምሁራን የሚወጡበት ክልል ተወዳዳሪ እንዳይሆን እየተደረገ ነው፣ ይህ ደግሞ ሕዝብን በዘላቂነት የሚጎዳ ነው ብለዋል። ትምህርትን መጉዳት የጠላትን አጀንዳ ማስፈጸም እንደኾነም አንስተዋል።

የሚዲያ እና የኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ ሀገር የሚለውጥ እና ትውልድን የሚታደግ ሥራ መሥራት እንደሚገባውም ገልጸዋል። በክልሉ ያለው ምዝገባ ተስፋ የሚሰጥ እና የተሻለ ነው ያሉት ኀላፊው ነገር ግን አሁንም ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ እንዲመዘገቡ ይፈለጋል ነው ያሉት። በተማሪዎች ምዝገባ ወደኋላ የቀሩትን አካባቢዎች በመደገፍ እንዲያስመዘግቡ ማድረግ ይገባል ብለዋል። ከዚህ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዲኾኑ መፍቀድ እንደማይገባም አሳስበዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Indirizzo

Sweedn
Rome

Sito Web

Notifiche

Lasciando la tua email puoi essere il primo a sapere quando Taytu ጣይቱ pubblica notizie e promozioni. Il tuo indirizzo email non verrà utilizzato per nessun altro scopo e potrai annullare l'iscrizione in qualsiasi momento.

Condividi